በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የተመራ የአመራር ቡድን በቡታጅራ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኘ
በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የተመራ የአመራር ቡድን በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝቷል፡፡
ቡድኑ የቡታጅራ ከተማ የኮሪደር ልማት፣ የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት እና የክላስተር ቢሮዎች ግንባታ አሁን ያለበትን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክቷል።
በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት እየተሰራ ያለው የቡታጅራ ከተማ የህዝብ ፋርማሲ 95 በመቶ መድረሱ ተመላክቷል።
የክልል ማዕከል ቢሮ ግንባታ መጓተቶች ቢኖሩትም አሁን ላይ ወደ ሰራ ተገብቶ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑ ተመላክቷል።
የኮሪደር ልማት ስራው በተያዘለት ዕቅድ እየሄደ መሆኑን የሱፐርቪዥን ቡድኑ ገምግሟል፡፡
በቡታጅራ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የከተማ ልማት ስራዎች ከተማዋ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝ አመላካች ነው ሲሉ አቶ ስንታየሁ በግብረ መልሳቸው አመላክተዋል።
ህብረተሰቡ በከተማ ልማት ስራዎች እያደረገ ያለው ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ያነሱት አቶ ስንታየሁ ይህን ተግባር ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አመላክተዋል።
የከተማ ልማት ስራዎች ዕውን እንዲሆኑ የማዘጋጃ ቤታዊ የገቢ አሰባሰብን ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ