ከተለያዩ ወረዳ፣ ከተማ አስተዳደር፣ ዞንና ክልል የተውጣጡ የነጋዴው ማህበረሰብ እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝትና ምልከታ አድርገዋል።
በቦንጋ ክላስተር ማዕከል ውስጥ እየተሰራ ያለው የሀኢት ዳቦና እንጀራ አምራችና አከፋፋይ የሥራ እንቅስቃሴ በተሳታፊዎች የተጎበኘ ሲሆን በተቋሙ አስተባባሪዎች ገለጻና ማብራሪያ ተደርጓል።
ሀኢት የዳቦና እንጀራ አምራችና አከፋፋይ ማህበር በቀን 200,000 ዳቦና 20 ሺህ እንጀራ ያመርታል ተብሏል።
በመቀጠልም የቅመማ ቅመም ማምረቻና ማከፋፈያም ጉብኝት ተደርጓል።
የቅመማ ቅመም ምርቶች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያዎች በመላክ አካባቢን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፋይዳው የላቀ እንደሆነም ተገልጿል።
በክላስተር ማዕከል እየተሰሩ ካሉት የሥራ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የእንጨትና የብሎከት ማምረቻ ሥራዎችም ተጎብኝተዋል።
የጉብኝቱ ተሣታፊዎችም ወደመጡበት አካባቢ ሲመለሱ ከጉብኝቱ ያገኙትን ተሞክሮ ተግባራዊ እንዲያደርጉ የኢኖቬሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛው ጋግያብ አሳስበዋል።
በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የበጀትና የክትትል ድጋፍ በ7 ሺ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የአረንጓዴ ፓርክና የኮርደር ልማት ጉብኝት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡ መለሰ ገብሬ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል