በክረምት ወራት የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ወጣቶች አልባሌ ስፍራ እንዳይውሉ ከማድረግ በተጓዳኝ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ እድል እየፈጠረ መሆኑ ተገለጸ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ሲካሄድ የቆየው የክረምት ወራት የእግር ኳስ ሻምፒዮና ተጠናቋል።
በከተማው በክረምት ወራት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የእግር ኳስ ሻምፒዮና በስምንት ቀበሌያት መካከል ሲደረግ ቆይቶ ፍፃሜውን አግኝቷል።
በማጠቃለያው መርሃግብር ላይ የተገኙት የከተማው ከንቲባ አቶ ብዙአየሁ ታደሰ በንግግራቸው፤ በከተማው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ተግባራት ሁለንተናዊ ልማት ለማምጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ እየደገፉ እንደሆነ ተናግረዋል።
በዘርፉ የተሳተፉትን አካላት ያመሰገኑት ከንቲባው፤ ስፖርቱ ህዝባዊ መሠረት ይዞ ውጤታማ እንዲሆን የከተማው አስተዳደር ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
የከተማው ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ዩኒት አስተባባሪ አቶ በረከት ፉላሳ ሻምፒዮናው ወጣቶች በክረምት ወራት ከአልባሌ ስፍራ አንዲታቀቡ ከማድረግ በተጓዳኝ ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ረገድ ውጤታማ እንደነበረ ገልጸዋል።
የፍፃሜ ጨዋታ በክቢቻ እና በቡሼ ቀበሌ መካከል የተደረገ ሲሆን ቡሼ አሸናፊ በመሆን ዋንጫ አንስቷል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግሥቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በክረምት ወራት የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ወጣቶች አልባሌ ስፍራ እንዳይውሉ ከማድረግ በተጓዳኝ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ እድል እየፈጠረ መሆኑ ተገለጸ

More Stories
በአርሰናል እንደ አዲስ ብርሃን የፈነጠቀው ክርስቶስ ጾሊስ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን