የህፃናት መብትና ደህንነት ተጠብቆ የነገ ሀገር ተረካቢ ለማድረግ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የጋራ ትብብር ወሳኝ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ
የክልሉ የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ የአፍሪካ ህጻናት ቀንን ምክንያት በማድረግ ለከፍተኛ ችግር ተጋላጭ የሆኑ ህጻናትን ለመደገፍ ያለመ የምክክር መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ካሰች ኤልያስ፤ በህፃናት ላይ የሚደርሰው ጾታዊ፣ ስነ-ልቦናዊና አካላዊ ጉዳቶችን ቀድሞ ለመከላከል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የህፃናት መብትና ደህንነታቸው ተጠብቆ የነገ ሀገር ተረካቢ ለማድረግ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የጋራ ትብብር ወሳኝ መሆኑን የቢሮ ኃላፊዋ ጠቁመዋል።
የመድረኩ ዋነኛ ዓላማ ለከፍተኛ ችግር ተጋላጭ የሆኑ ህጻናትን ለመደገፍ እንዲሁም በህጻናት ጥበቃ እና ጉዲፈቻ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
በመድረኩ የቢሮ ኃላፊዎች፣ የሁሉም ዞኖች ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሞዴል ዕድር መሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ