በየተቋማቱ በኤችአይቪ ኤድስ መከላከል ዙሪያ የሚፈጠሩ ግንዛቤዎችን በማሳደግ የበጀትና ተያያዥ ችግሮችን መፍታት ላይ ሊተኮር እንደሚገባ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ላሉ ለየተቋማቱ ፎካል ፐርሰን የስልጠናና ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ አካሂዷል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል ወ/ሮ ሠራዊት ሰላቶ፣ አቶ ዘውዴ ባልቻና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት ውይይቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ያየንበትና ለቀጣይ ተግባር ግብዓት ያገኘንበት ስልጠናና ውይይት እንደሆነ ገልፀዋል።
አክለውም የኤች አይ ቪ ኤድስ ሥርጭት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ከአመራሩ ትኩረት መስጠት ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች በሚፈጠሩ የግንዛቤ ሥራዎች ለውጦች እየመጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ በቀጣይ በዘርፉ ከስልጠና ጀምሮ የኮንዶም እጥረት፣ 0.5 የኤች አይ ቪ በጀት በኮድ በየተቋማቱ አለመሆንና አለመጠቀም፣ በባለቤትነት የክትትል ሥርዓት አለመጠናከርና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን በቅንጅት መፍታት ላይ ሊተኮር እንደሚገባ አንስተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና ዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቲዎስ ጋርሾ፤ ሀገር በቀል የፋይናንስ ሥርዓትን በመከተል በኤች አይ ቪ ዘርፍ ከሰው ኃይል ጀምሮ የሜይንስትሪሚንግ ሥራዎችን ለማሳለጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ተነጋግሮ በቅንጅት በመፍታት በዳታ ሲስተም በመታገዝ የመረጃ ተዓማኒነትና ጥራትን መሠረት በማድረግ የሚስራ ይሆናል ብለዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ