በየተቋማቱ በኤችአይቪ ኤድስ መከላከል ዙሪያ የሚፈጠሩ ግንዛቤዎችን በማሳደግ የበጀትና ተያያዥ ችግሮችን መፍታት ላይ ሊተኮር እንደሚገባ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ላሉ ለየተቋማቱ ፎካል ፐርሰን የስልጠናና ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ አካሂዷል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል ወ/ሮ ሠራዊት ሰላቶ፣ አቶ ዘውዴ ባልቻና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት ውይይቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ያየንበትና ለቀጣይ ተግባር ግብዓት ያገኘንበት ስልጠናና ውይይት እንደሆነ ገልፀዋል።
አክለውም የኤች አይ ቪ ኤድስ ሥርጭት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ከአመራሩ ትኩረት መስጠት ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች በሚፈጠሩ የግንዛቤ ሥራዎች ለውጦች እየመጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ በቀጣይ በዘርፉ ከስልጠና ጀምሮ የኮንዶም እጥረት፣ 0.5 የኤች አይ ቪ በጀት በኮድ በየተቋማቱ አለመሆንና አለመጠቀም፣ በባለቤትነት የክትትል ሥርዓት አለመጠናከርና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን በቅንጅት መፍታት ላይ ሊተኮር እንደሚገባ አንስተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና ዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቲዎስ ጋርሾ፤ ሀገር በቀል የፋይናንስ ሥርዓትን በመከተል በኤች አይ ቪ ዘርፍ ከሰው ኃይል ጀምሮ የሜይንስትሪሚንግ ሥራዎችን ለማሳለጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ተነጋግሮ በቅንጅት በመፍታት በዳታ ሲስተም በመታገዝ የመረጃ ተዓማኒነትና ጥራትን መሠረት በማድረግ የሚስራ ይሆናል ብለዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል