ሀዋሳ፡ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የተቀናጀ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ መፍጠር ለሀገር ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ ገ/መስቀል ጫላ ገለጹ፡፡
ሚዲያ በእውነትና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ መረጃዎችን ለህዝቡ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት ተመላክቷል።
“የድህረ እውነት ዘመንን በእውነትና በእውቀት” በሚል መሪ ሀሳብ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎችና አመራር አካላት በወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፖርቲ ቅረንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በንግግራቸው “የተቀናጀ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ መፍጠር ለሀገር ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚዲያ በእውነትና በእውቀት የተመሰረተ ተጨባጭ መረጃዎችን ለህዝቡ ተደራሽ ከማድረግ አኳያም የበኩሉን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
የውሽት ትርክት ለማጥፋት ሚዲያ ትልቅ ድረሻ አለው በማለት ሀገሪቱን በሰለጠነ መረጃ ለማበልፀግ ከዚህ ቀደም በተሰራው ሥራ ለውጥ መመዝገቡን ጠቁመዋል።
ህዝቡ ለሰላም፣ ለልማትና ለዴሞክራሲ በማነሳሳት በኩል ሚዲያ ከፍተኛ አስተዋዕጾ በማድረግ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን አክለዋል።
ሚዲያ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ከማጎልበት አኳያ ወቅቱን የሚመጥን መረጃ በማቅረብ በለውጡ ትሩፋት የተገኙ ውጤቶች በሚገባ ልክ ከማስተዋወቅ ረገድም ሀላፊነት መወጣት አለባቸው ብለዋል።
በድህረ እውነት ወቅት ላይ እንገኛለን ያሉት የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ፈዲላ ቢያ ሚዲያ የህዝቦች ማህበራዊ መሰረት ለመገንባት ትልቅ ድረሻ አለው ብለዋል።
ሚዲያ የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ጠቃሚና ትኩስ መረጃዎችን እንዲሁም ችግር ፈች የሆኑ መረጃዎች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
የስልጠናው ዋነኛው ዓላማ ከመረጃ ወቅታዊነት ጋር ተያይዘው ጠንካራ የሚዲያ ባለሙያዎችን መፍጠርና ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁ በማድረግ በቀጣይ ዓመታት አመርቂ ድሎችን ለማስመዝገብ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ
“የብልጽግና ጉዞአችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ የንግዱ ማሕበረሰብ ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
በዞኑ ኩረጃን የሚፀየፍ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ