ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓመታዊ አገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በመተባበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃለፊዎች፣ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የሙያ ማህበራት ተሳትፈዋል ።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሁለት ዓመታት የመመሰጋገን ቀን ማክበሩ የሚታወስ ሲሆን የዘንድሮው ዓመታዊ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን “ተማሪዎች ለሀገር ሰላም ናቸው” በሚል መሪ ቃል ነው እየተከበረ የሚገኘው።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ