ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓመታዊ አገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በመተባበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃለፊዎች፣ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የሙያ ማህበራት ተሳትፈዋል ።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሁለት ዓመታት የመመሰጋገን ቀን ማክበሩ የሚታወስ ሲሆን የዘንድሮው ዓመታዊ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን “ተማሪዎች ለሀገር ሰላም ናቸው” በሚል መሪ ቃል ነው እየተከበረ የሚገኘው።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ
More Stories
በመጀመሪያ 3 ወራት የቅድመ ወሊድ አገልግሎት በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ተጠናክሮ ሊሰራበት እንደሚገባ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ
ምስራቅ አፍሪካን ያመሰው ክስተት
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከማጠናከር ባለፈ ጤናማ ንቁና የተሻለ ስብዕና ያለው ትውልድ ለመፍጠር የቴኳንዶ ስፖርት ትልቅ ሚና እንዳለው ተመላከተ