ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓመታዊ አገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በመተባበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃለፊዎች፣ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የሙያ ማህበራት ተሳትፈዋል ።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሁለት ዓመታት የመመሰጋገን ቀን ማክበሩ የሚታወስ ሲሆን የዘንድሮው ዓመታዊ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን “ተማሪዎች ለሀገር ሰላም ናቸው” በሚል መሪ ቃል ነው እየተከበረ የሚገኘው።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
በቡና ዘርፍ ያለውን ህገወጥ ንግድ በጋራ መግታት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የቡና ማህበር ገለጸ
6ኛው ሀገር አቀፍ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ኮንፍረንስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በአብዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም እየተካሄደ ነው
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መንግስት በከተማና በገጠር ለጀመራቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ዋነኛ ሞተሮች ናቸው – አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)