ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓመታዊ አገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በመተባበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃለፊዎች፣ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የሙያ ማህበራት ተሳትፈዋል ።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሁለት ዓመታት የመመሰጋገን ቀን ማክበሩ የሚታወስ ሲሆን የዘንድሮው ዓመታዊ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን “ተማሪዎች ለሀገር ሰላም ናቸው” በሚል መሪ ቃል ነው እየተከበረ የሚገኘው።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
ግንቦት 24 የሚካሄደውን ጠቅላላ ምርጫን ምከንያት በማድረግ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን በወላይታ ዞን የኪንዶ ድዳየ ወረዳ ወጣቶች ገለጹ