ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የበጎ ፈቃድ ሥራን ባህል ልናደርግ ይገባል ሲል አስታውቋል፡፡
በዘንድሮ ክረምት ለወጣቶች በጎ ፈቃድ ሥራ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ለመሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳግም ጃምቦ፥ ለክረምት በጎ ፈቃድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ኮሚቴ በማዋቀር ተቋማት የየራሳቸውን ዕቅድ እንዲያቀርቡ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት በ13 ዘርፎች ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በተለያዩ በጎ ተግባራት የተሳተፉ ሲሆን በዘንድሮው ክረምት ሥራ ክልሉ በሚያቀርበው ዕቅድ መነሻ ለማሰማራት ዝግጅት መደርጉን ኃላፊው ገልጸዋል።
የአረጋውያንን ቤት ማደስ፣ የተበላሹ መንገዶችን መጠገን፣ ማዕድ ማጋራት ከአምናው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ በዘንድሮው ክረምት ደግሞ ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ለመድረስ እና የተሻለ ለመሥራት መታሰቡ ተጠቁሟል።
የበጎ ፈቃድ ሥራ በክረምት ወቅት ለወጣቶች ብቻ የሚተው ባለመሆኑ፥ ሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሠራ እንደሆነና ህብረተሰቡ በጎ ሥራን ባህሉ ማድረግ እንዳለበት ነው አቶ ዳግም የገለፁት።
ከበጎ ፈቃድ ሥራው ባሻገር የክረምት ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና በተለየዩ የስፖርት ዓይነቶች እንደሚካሄድ እና የአማሮ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እንደገና በማነቃቃት ወደ ቀድሞ አቋሙ የመመለስ ሥራ እንደሚሠራም ተመልክቷል።
ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ – ከፍስሃገነት ጣቢያችን
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ