ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የበጎ ፈቃድ ሥራን ባህል ልናደርግ ይገባል ሲል አስታውቋል፡፡
በዘንድሮ ክረምት ለወጣቶች በጎ ፈቃድ ሥራ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ለመሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳግም ጃምቦ፥ ለክረምት በጎ ፈቃድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ኮሚቴ በማዋቀር ተቋማት የየራሳቸውን ዕቅድ እንዲያቀርቡ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት በ13 ዘርፎች ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በተለያዩ በጎ ተግባራት የተሳተፉ ሲሆን በዘንድሮው ክረምት ሥራ ክልሉ በሚያቀርበው ዕቅድ መነሻ ለማሰማራት ዝግጅት መደርጉን ኃላፊው ገልጸዋል።
የአረጋውያንን ቤት ማደስ፣ የተበላሹ መንገዶችን መጠገን፣ ማዕድ ማጋራት ከአምናው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ በዘንድሮው ክረምት ደግሞ ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ለመድረስ እና የተሻለ ለመሥራት መታሰቡ ተጠቁሟል።
የበጎ ፈቃድ ሥራ በክረምት ወቅት ለወጣቶች ብቻ የሚተው ባለመሆኑ፥ ሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሠራ እንደሆነና ህብረተሰቡ በጎ ሥራን ባህሉ ማድረግ እንዳለበት ነው አቶ ዳግም የገለፁት።
ከበጎ ፈቃድ ሥራው ባሻገር የክረምት ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና በተለየዩ የስፖርት ዓይነቶች እንደሚካሄድ እና የአማሮ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እንደገና በማነቃቃት ወደ ቀድሞ አቋሙ የመመለስ ሥራ እንደሚሠራም ተመልክቷል።
ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ – ከፍስሃገነት ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ