ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የበጎ ፈቃድ ሥራን ባህል ልናደርግ ይገባል ሲል አስታውቋል፡፡
በዘንድሮ ክረምት ለወጣቶች በጎ ፈቃድ ሥራ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ለመሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የአማሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳግም ጃምቦ፥ ለክረምት በጎ ፈቃድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ኮሚቴ በማዋቀር ተቋማት የየራሳቸውን ዕቅድ እንዲያቀርቡ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት በ13 ዘርፎች ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በተለያዩ በጎ ተግባራት የተሳተፉ ሲሆን በዘንድሮው ክረምት ሥራ ክልሉ በሚያቀርበው ዕቅድ መነሻ ለማሰማራት ዝግጅት መደርጉን ኃላፊው ገልጸዋል።
የአረጋውያንን ቤት ማደስ፣ የተበላሹ መንገዶችን መጠገን፣ ማዕድ ማጋራት ከአምናው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ በዘንድሮው ክረምት ደግሞ ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ለመድረስ እና የተሻለ ለመሥራት መታሰቡ ተጠቁሟል።
የበጎ ፈቃድ ሥራ በክረምት ወቅት ለወጣቶች ብቻ የሚተው ባለመሆኑ፥ ሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሠራ እንደሆነና ህብረተሰቡ በጎ ሥራን ባህሉ ማድረግ እንዳለበት ነው አቶ ዳግም የገለፁት።
ከበጎ ፈቃድ ሥራው ባሻገር የክረምት ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና በተለየዩ የስፖርት ዓይነቶች እንደሚካሄድ እና የአማሮ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እንደገና በማነቃቃት ወደ ቀድሞ አቋሙ የመመለስ ሥራ እንደሚሠራም ተመልክቷል።
ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ – ከፍስሃገነት ጣቢያችን
More Stories
በተቋማትና በባለሙያዎች መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ