ሀዋሳ፡ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኦሞ ባንክ አርሶ አደሩን እና በተለያዩ የንግድ የስራና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የህበረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን በካፋ ዞን የኦሞ ባንክ ጠሎ ቅርንጫፍ አስታውቋል።
ባንኩ የአሰራር ስርዓቱን በማዘመን የደንበኞችን ቁጥር እያሳደገ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በጠሎ ወረዳ የኦሞ ባንክ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰጋኸኝ አበበ እንደገለጹት፤ ባንኩ ወደ ባንክ ደረጃ ከመሸጋገሩ በፊት ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ ለአካባቢው ማህበረሰብ የብድር አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን የኢኮኖሚ ችግር ሲቀርፍ ቆይቷል።
በአሁን ወቅት ባንኩ ከብሄራዊ ባንክ በተሰጠው ፈቃድ መሰረት የአሰራር ስዓቱን በማሻሻል በባንክ በመደራጀት ከብድር ስርጭት በተጨማሪ ደንበኞች በባንኩ እንዲቆጥቡና ገንዘብ እንዲያንቀሳቅሱ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
ባንኩ በተያዘው በጀት አመት ከ1መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ማስጠቆብ መቻሉን የገለፁት ሀላፊው ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የብድር አገልግሎት መስጠት መቻሉንም ገልፀዋል።
በድለባ፣ በከተማ ግብርናና በተለያዩ የንግድ ስራዎች ለተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ባንኩ የብድር አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የገለጹት አቶ አሰጋኸኝ ከዚህ ቀደም ከተቋሙ የብድር አገልግሎት ወስደው ያልመለሱ ማህበራት የወሰዱትን ብድር የማስመለስ ስራ በወረዳው ከተቋቋመው ግብረ-ሃይል ጋር በመሆን እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ማስመለስ የተቻለ ሲሆን ይህ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል አቶ አሰጋኸኝ።
የባንኩ ደንበኞች በበኩላቸው ባንኩ ባደረገው ማስተካካከያ መደሰታቸውን በመግለጽ ከቁጠባ በተጨማሪ ከባንኩ የብድር አገልግሎት በማግኘት ኑሯቸውን ለማሻሻል ማቀዳቸውን ነው የገለፁት።
ባንኩ ለአርሶ አደሮችና ለወጣቶች የፋይናንስ ምንጭ በመሆን ሥራ አጥነትን በመቀነስና ቁጠባን ባህል በማድረግ ረገድ ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን
More Stories
በተቋማትና በባለሙያዎች መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ