ሀዋሳ፡ ግንቦት 02/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ “አንድነትና ህብረት ለባስኬቶ ከፍታና ለህዝቦች ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ውይይቱ ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ በፌደራልና በክልል በተለያየ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የሚገኙ የባስኬቶ ዞን ተወላጆች፣ የባስኬቶ ዞን የሶስቱም መዋቅር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።
የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ህዝቡ እርስ በርስ ትስስር የሚፈጥርበት እና በአካባቢው እድገትና ልማቶች ዙሪያ በመግባባት ወደ ተግባር የሚገባበት ነው ብለዋል።
ለዘላቂ አንድነትና ህብረት መሠረት በመጣል ለላቀ ሥራ በቁጭት መቆም የሚያስችልና ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ ያለመ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በመሆኑም አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ መተሳሰብ ላይ የጋራ ሥምምነት መፍጠር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
በመድረኩ በዞኑ በሁሉም ማህበረሰብ ክፍሎች በየደረጃው የተካሄዱ ውይይቶች ዙሪያ የተዘጋጀ የማጠቃለያ ሰነድ ለውይይት ቀርቧል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት 2 ሺህ 273 መዝገቦች በዐቃቤ ህግ ውሳኔ ማግኘታቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት አጋር ተቋማት ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናገሩ
የተፈጠረላቸውን የሥራ ዕድል ተጠቅመው በመሥራታቸው የተሻለ ለውጥ እያገኙ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ወጣቶች ተናገሩ