ሀዋሳ፡ ግንቦት 02/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ “አንድነትና ህብረት ለባስኬቶ ከፍታና ለህዝቦች ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ውይይቱ ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ በፌደራልና በክልል በተለያየ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የሚገኙ የባስኬቶ ዞን ተወላጆች፣ የባስኬቶ ዞን የሶስቱም መዋቅር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።
የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ህዝቡ እርስ በርስ ትስስር የሚፈጥርበት እና በአካባቢው እድገትና ልማቶች ዙሪያ በመግባባት ወደ ተግባር የሚገባበት ነው ብለዋል።
ለዘላቂ አንድነትና ህብረት መሠረት በመጣል ለላቀ ሥራ በቁጭት መቆም የሚያስችልና ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ ያለመ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በመሆኑም አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ መተሳሰብ ላይ የጋራ ሥምምነት መፍጠር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
በመድረኩ በዞኑ በሁሉም ማህበረሰብ ክፍሎች በየደረጃው የተካሄዱ ውይይቶች ዙሪያ የተዘጋጀ የማጠቃለያ ሰነድ ለውይይት ቀርቧል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የአርሶ አደሩን የመሬት ሀብት ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶች ጤናና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ2018 ባጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል
የከተማ አስተዳደሩ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ቤት ወጣቶችን በማህበር በማደራጀት የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ