የቡርጂ ዞን አስተዳደር፣ የዞኑ ሴቶችና ህጻናት ዩኒት፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ዩኒት እና የወጣቶች ክንፍ በሶያማ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የማዕድ ማጋራት ስነ-ስርዓት አከናውነዋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳኜ ህዶ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ድጋፍ የተደረገው በተለያዩ መስሪያ ቤቶች እንደሆነና ወጣቶች ማህበረሰቡን በማስተባበር ያደረጉት በመሆኑ ትልቁን ድርሻ ይወስዳሉ ብለዋል።
ለአቅመ ደካሞች በበዓል ወቅት ብቻ ሳይሆን በሌሎች ጊዜያትም ድጋፉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በቀጣይ በቋሚነት የሚደገፉበትና ስራ የሚያገኙበት አግባብ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የቡርጂ ዞን ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ማሪያም ሲሳይ፤ የተደረገው ድጋፍ ከጎናችሁ መሆናችንን ማሳያ ነው በማለት ይህም አንድነት እና አብሮነትን እንደሚያጠናክር አስረድተዋል።
በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን የገለጹት ወ/ሮ ወለተኪዳን ገ/እግዚአብሔር እና ወ/ሮ ታፈሰች ታደሰ፤ መንግስትና ህዝብ ከጎናቸው እንደሆኑ በማሳየታቸው አመስግነዋል።
አቶ ወየሳ ማሞ የሶያማ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ በፊት በርካታ ድጋፎች ሲደረጉላቸው መቆየቱን በማንሳት ለህክምና እንዲሁም በቋሚነት ስራ እንዲሰሩ የተመቻቸላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
2ኛ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው
የሚገነቡ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማስቻል ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ከተሞችን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ ውብና ምቹ ለማድርግ በቆሻሻ አወጋገድና አያያዝ ሥርዓት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረት ልማት ቢሮ አሳሰበ