ለትምህርት ልማት ጥራት የተሰጠው ትኩረት ለውጥ እያስመዘገበ እንደሚገኝ ያብራሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየመድረኮቹ የሚተላለፉና ውሳኔ የሚተላልፍባቸው መልዕክቶች ለዘርፉ ውጤት ትልቅ አቅም እየፈጠረ ነው ብለዋል።
የትምህርት ለትውልድ ዋና መልዕክት ትምህርት ቤቶችን ማሳደግ፣ ማስዋብና ለተማሪዎች ማራኪ ማድረግ ዘርፉ ቀጣይነት ያለው ውጤት እንዲያስመዘግብ ትኩረት መስጠት ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መላው ህዝብ ለዘርፉ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
በመድረኩ የተገኙ አመራሮችና የሙያው ባለቤት የሆኑ የትምህርት ልማት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች የተጣለባቸውን ሀላፊነት በትጋት እንዲወጡም አቶ ጥላሁን አሳስበዋል።
ጉባኤው ባለፉት ጊዜያት የተከናወኑ ተግባራት የሚገመገሙበት፣ በድክመት የተመዘገቡትን በመለየት በቁጭት ለቀጣይ ዕቅድ የሚከለስበት መሆን አለበት ብለዋል።
የአንድን ሀገር ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ ትምህርት ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ፤ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለመፍጠር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
ከትምህርት ተደራሽነት አኳያ ሰፊ ሥራ የተሠራ ቢሆንም ከጥራት አንፃር ሰፊ ክፍተት ያለበት በመሆኑ ችግሩ ተለይቶ ከዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ከመላው ህዝብ ጋር በመቀናጀት እየተሠራ እንዳለም ገልፀዋል ወ/ሮ ፀሐይ።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ፤ እንግዶችን በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ተቀብለው ትምህርት የሁሉም ልማት መሠረት ነው ብለዋል።
በዕውቀትና በክህሎት የተሻለ ዜጋን ለመፍጠር ዘርፉን መደገፍ፣ በቁርጠኝነት መሥራትና ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቃል ተብሏል።
በመድረኩ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እየቀረበ ነው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ