በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ከነዚህ መካከልም 7ሺህ 942 ተማሪዎች በበይነ መረብ ፈተናውን እንደሚፈተኑ ተጠቁሟል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳያስ እንድሪያስ በክልሉ 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በ2016፥ 1ሺህ 958 ተፈታኞች በበይነ መረብ ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመው፥ ዘንድሮ 7ሺህ 942 ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በተያዘው የትምህርት ዘመንም ብቁ፣ ተወዳዳሪ እና ተስፈኛ ተፈታኞችን በማህበራዊና በተፈጥሮ ሳይንስ ለማስፈተን ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱን አብራርተዋል።
እነዚህ ተማሪዎች በክልሉ በሚገኙ 57 ትምህርቶ ቤቶች እና በ4ቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን እንደሚወስዱና ለዚህም ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ጭምር አቶ ኢሳያስ ጠቁመዋል።
የቀድሞ የምዘና ስርዓት የጋሸበና ኋላ ቀር እንደነበረ ያስታወሱት ኃላፊው፥ ዘንድሮ ያሉ ጉድለቶችን ለማረም በየደረጃ ከሚገኙ አካላት ጋር ውይይት መደረጉን ጭምር አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ