በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ከነዚህ መካከልም 7ሺህ 942 ተማሪዎች በበይነ መረብ ፈተናውን እንደሚፈተኑ ተጠቁሟል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳያስ እንድሪያስ በክልሉ 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በ2016፥ 1ሺህ 958 ተፈታኞች በበይነ መረብ ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመው፥ ዘንድሮ 7ሺህ 942 ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በተያዘው የትምህርት ዘመንም ብቁ፣ ተወዳዳሪ እና ተስፈኛ ተፈታኞችን በማህበራዊና በተፈጥሮ ሳይንስ ለማስፈተን ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱን አብራርተዋል።
እነዚህ ተማሪዎች በክልሉ በሚገኙ 57 ትምህርቶ ቤቶች እና በ4ቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን እንደሚወስዱና ለዚህም ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ጭምር አቶ ኢሳያስ ጠቁመዋል።
የቀድሞ የምዘና ስርዓት የጋሸበና ኋላ ቀር እንደነበረ ያስታወሱት ኃላፊው፥ ዘንድሮ ያሉ ጉድለቶችን ለማረም በየደረጃ ከሚገኙ አካላት ጋር ውይይት መደረጉን ጭምር አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት 2 ሺህ 273 መዝገቦች በዐቃቤ ህግ ውሳኔ ማግኘታቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት አጋር ተቋማት ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናገሩ
የተፈጠረላቸውን የሥራ ዕድል ተጠቅመው በመሥራታቸው የተሻለ ለውጥ እያገኙ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ወጣቶች ተናገሩ