በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ከነዚህ መካከልም 7ሺህ 942 ተማሪዎች በበይነ መረብ ፈተናውን እንደሚፈተኑ ተጠቁሟል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳያስ እንድሪያስ በክልሉ 57 ሺህ 241 ተማሪዎች የ2017 ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለመፈተን መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በ2016፥ 1ሺህ 958 ተፈታኞች በበይነ መረብ ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመው፥ ዘንድሮ 7ሺህ 942 ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በተያዘው የትምህርት ዘመንም ብቁ፣ ተወዳዳሪ እና ተስፈኛ ተፈታኞችን በማህበራዊና በተፈጥሮ ሳይንስ ለማስፈተን ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱን አብራርተዋል።
እነዚህ ተማሪዎች በክልሉ በሚገኙ 57 ትምህርቶ ቤቶች እና በ4ቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን እንደሚወስዱና ለዚህም ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ጭምር አቶ ኢሳያስ ጠቁመዋል።
የቀድሞ የምዘና ስርዓት የጋሸበና ኋላ ቀር እንደነበረ ያስታወሱት ኃላፊው፥ ዘንድሮ ያሉ ጉድለቶችን ለማረም በየደረጃ ከሚገኙ አካላት ጋር ውይይት መደረጉን ጭምር አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል