ግሎባል ፋይናንስ ባካሄደው የ2025 ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ የባንኮች ውድድር አዋሽ ባንክ ከ36 የአፍሪካ ምርጥ ባንኮች አንዱ በመሆን እውቅና ማገኘቱ ተገለፀ
የባንኩ ሲኒየር ቺፍ ማርኬቲንግ ኦፊሰር አቶ ዮሐንስ መርጋ እውቅናውን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አዋሽ ባንክ እ.አ.አ በ2025 ግሎባል ፋይናንስ ባካሄደው ዓለም አቀፍ የባንኮች ውድድር አዋሽ ባንክ ከአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ባንክ ተብለው ከተመረጡ 36 ባንኮች መካከል አንዱ በመሆን ከኢትዮጵያ ብቸኛው ባንክ ሆኖ ለ4ኛ ጊዜ መመረጡን አስታውቀዋል።
አዋሽ ባንክ የዓመቱ ምርጥ ባንኮችን በመቀላቀል ዕውቅና ለማግኘት የቻለው የዓመታዊ ትርፍ፣ በብድር አቅርቦት መጠን፣ በትርፍ ክፍፍል ተደራሽነት፣ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እና ባንኩ ለደንበኞቹ በሚሰጠው አገልግሎት፣ በደንበኞች ብዛትና በገበያ ድርሻ ዕድገት፣ ዘመኑን በሚዋጁ አዳዲስ አገልግሎቶች የመሳሰሉትን የግሎባል ፋይናንስ የማወዳደሪያ መስፈርቶችን በማሟላቱ እንደሆነ አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል።
አቶ ዮሐንስ አክለውም የተለያዩ የፋይናንስ ዘርፍ ተንታኞችና ሌሎችም የዘርፉ ባለሙያዎች ለአዋሽ ባንክ የሰጡት ድምፅ ለባንኩ ዕውቅና ማግኘት ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንደነበረው ተናግረዋል።
አዋሽ ባንክ ያገኘው እውቅና በኢትዮጵያ የባንኮች ዘርፍ መነቃቃትን የሚፈጥርና ሌሎች ባንኮች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
ዘጋቢ፤- ንጋቱ ወልዴ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ