4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና ይሰጣቸዋል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና እንደሚሰጣቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስታወቁ።
በዚህ ዙሪያ መግለጫ የሰጡት ኃላፊው፤ የግብረገብ ትምህርት በክልሉ በ2016 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን አብራርተዋል።
የግብረገብ ትምህርት የተማሪዎችን ስነ ምግባር በመቅረፅ ለቀጣይ ህይወታቸው መደላድል ስለሚሆን በዕውቀት የተመራ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ስለዚህም በክልሉ በሁሉም ማዕከላት 4 ሺህ 972 መምህራን የመማር ማስተማር ስልጠናውን ይወስዳሉ ብለዋል።
የግብረገብ ትምህርት ተማሪዎች ከመምህራን ጋር ለሚኖራቸው መልካም መስተጋብር ስለሚፈጥር ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ስልጠናው የግብረገብ ትምህርት መፅሀፍት ባዘጋጁ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚሰጥ ሲሆን የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት መምህራን ተሳታፊ ይሆናሉ።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
“ትንንሽ የሚመስሉ ስራዎች ለትልልቅ ዕድሎች በር ይከፍታሉ” – ወይዘሮ ህልውና ጌታቸው
የህግ ታራሚዎችን በስነ ምግባር ለማነፅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለፀ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠቀ