4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና ይሰጣቸዋል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና እንደሚሰጣቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስታወቁ።
በዚህ ዙሪያ መግለጫ የሰጡት ኃላፊው፤ የግብረገብ ትምህርት በክልሉ በ2016 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን አብራርተዋል።
የግብረገብ ትምህርት የተማሪዎችን ስነ ምግባር በመቅረፅ ለቀጣይ ህይወታቸው መደላድል ስለሚሆን በዕውቀት የተመራ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ስለዚህም በክልሉ በሁሉም ማዕከላት 4 ሺህ 972 መምህራን የመማር ማስተማር ስልጠናውን ይወስዳሉ ብለዋል።
የግብረገብ ትምህርት ተማሪዎች ከመምህራን ጋር ለሚኖራቸው መልካም መስተጋብር ስለሚፈጥር ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ስልጠናው የግብረገብ ትምህርት መፅሀፍት ባዘጋጁ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚሰጥ ሲሆን የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት መምህራን ተሳታፊ ይሆናሉ።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ