4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና ይሰጣቸዋል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና እንደሚሰጣቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስታወቁ።
በዚህ ዙሪያ መግለጫ የሰጡት ኃላፊው፤ የግብረገብ ትምህርት በክልሉ በ2016 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን አብራርተዋል።
የግብረገብ ትምህርት የተማሪዎችን ስነ ምግባር በመቅረፅ ለቀጣይ ህይወታቸው መደላድል ስለሚሆን በዕውቀት የተመራ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ስለዚህም በክልሉ በሁሉም ማዕከላት 4 ሺህ 972 መምህራን የመማር ማስተማር ስልጠናውን ይወስዳሉ ብለዋል።
የግብረገብ ትምህርት ተማሪዎች ከመምህራን ጋር ለሚኖራቸው መልካም መስተጋብር ስለሚፈጥር ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ስልጠናው የግብረገብ ትምህርት መፅሀፍት ባዘጋጁ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚሰጥ ሲሆን የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት መምህራን ተሳታፊ ይሆናሉ።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ