4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና ይሰጣቸዋል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 4 ሺህ 972 የግብረገብ መምህራን ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጠና እንደሚሰጣቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስታወቁ።
በዚህ ዙሪያ መግለጫ የሰጡት ኃላፊው፤ የግብረገብ ትምህርት በክልሉ በ2016 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን አብራርተዋል።
የግብረገብ ትምህርት የተማሪዎችን ስነ ምግባር በመቅረፅ ለቀጣይ ህይወታቸው መደላድል ስለሚሆን በዕውቀት የተመራ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ስለዚህም በክልሉ በሁሉም ማዕከላት 4 ሺህ 972 መምህራን የመማር ማስተማር ስልጠናውን ይወስዳሉ ብለዋል።
የግብረገብ ትምህርት ተማሪዎች ከመምህራን ጋር ለሚኖራቸው መልካም መስተጋብር ስለሚፈጥር ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ስልጠናው የግብረገብ ትምህርት መፅሀፍት ባዘጋጁ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚሰጥ ሲሆን የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት መምህራን ተሳታፊ ይሆናሉ።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል