ቢሮው “ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማወዳደር ነው ያለመው ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ እንዳሉት በክህሎት ፣ በቴክኖሎጂና በጥናትና ምርምር ሥራዎች ውድድር ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል ።
በክልል ደረጃ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎች አልፈው በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚወዳደሩ ገልፀዋል ።
ይህ ውድድር በመካከለኛ የሰለጠነ የሰው ኃይል ከፍ ለማድረግና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ ኑሮን ለማሻሻል ተልሞ የሚሠራ መሆኑን አክለዋል ።
በክህሎት ልማት በ20 ሙያዎች 61 ሰልጣኞች ፣ በሰልጣኝ 4 ክላስተር ፣ በአሰልጣኝ 6 ክላስተር እንዲሁም በእንተርፕራይዝ ደረጃ 14 ቴክኖሎጂዎች የሚቀርቡ ይሆናሉ ብለዋል ።
በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች የተጠኑ 6 የምርምር ውጤቶች ይቀርባሉ ፡፡
ዘጋቢ፡ሰሎሞን አላሶ-ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን
More Stories
“ትንንሽ የሚመስሉ ስራዎች ለትልልቅ ዕድሎች በር ይከፍታሉ” – ወይዘሮ ህልውና ጌታቸው
የህግ ታራሚዎችን በስነ ምግባር ለማነፅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለፀ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠቀ