ቢሮው “ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማወዳደር ነው ያለመው ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ እንዳሉት በክህሎት ፣ በቴክኖሎጂና በጥናትና ምርምር ሥራዎች ውድድር ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል ።
በክልል ደረጃ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎች አልፈው በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚወዳደሩ ገልፀዋል ።
ይህ ውድድር በመካከለኛ የሰለጠነ የሰው ኃይል ከፍ ለማድረግና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ ኑሮን ለማሻሻል ተልሞ የሚሠራ መሆኑን አክለዋል ።
በክህሎት ልማት በ20 ሙያዎች 61 ሰልጣኞች ፣ በሰልጣኝ 4 ክላስተር ፣ በአሰልጣኝ 6 ክላስተር እንዲሁም በእንተርፕራይዝ ደረጃ 14 ቴክኖሎጂዎች የሚቀርቡ ይሆናሉ ብለዋል ።
በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች የተጠኑ 6 የምርምር ውጤቶች ይቀርባሉ ፡፡
ዘጋቢ፡ሰሎሞን አላሶ-ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል