ቢሮው “ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማወዳደር ነው ያለመው ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ እንዳሉት በክህሎት ፣ በቴክኖሎጂና በጥናትና ምርምር ሥራዎች ውድድር ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል ።
በክልል ደረጃ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎች አልፈው በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚወዳደሩ ገልፀዋል ።
ይህ ውድድር በመካከለኛ የሰለጠነ የሰው ኃይል ከፍ ለማድረግና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ ኑሮን ለማሻሻል ተልሞ የሚሠራ መሆኑን አክለዋል ።
በክህሎት ልማት በ20 ሙያዎች 61 ሰልጣኞች ፣ በሰልጣኝ 4 ክላስተር ፣ በአሰልጣኝ 6 ክላስተር እንዲሁም በእንተርፕራይዝ ደረጃ 14 ቴክኖሎጂዎች የሚቀርቡ ይሆናሉ ብለዋል ።
በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች የተጠኑ 6 የምርምር ውጤቶች ይቀርባሉ ፡፡
ዘጋቢ፡ሰሎሞን አላሶ-ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት 2 ሺህ 273 መዝገቦች በዐቃቤ ህግ ውሳኔ ማግኘታቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት አጋር ተቋማት ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናገሩ
የተፈጠረላቸውን የሥራ ዕድል ተጠቅመው በመሥራታቸው የተሻለ ለውጥ እያገኙ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ወጣቶች ተናገሩ