ሀዋሳ፡ መጋቢት 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የመጋቢታዊያን ፍሬዎች እና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል በጌዴኦ ዞን የፐብሊክ ሰርቫንት ብልጽግና ፓርቲ ህብረት ውይይት ተካሂዷል፡፡
የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ ምህረቱ ተፈሪ እንዳሉት፤ ብልጽግና ፓርቲ በፈተናዎች መካከል ተወልዶ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የለውጥ ፍሬ የተበሰረበት መጋቢት ወር ነው።
መጋቢት ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ሥልጣን የመጡት፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በራስ አቅም ልጆቿን አስተባብራ መሥራት እንደምትችል ያረጋገጠችበትና ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ እንደደረሰች የጠቁሙት አቶ ምህረቱ፤ እነዚህ ሁነቶች የመጋቢታዊያን ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ፈተናዎችን ወደ ዕድል ቀይረው በርካታ የመጋቢታዊያን ፍሬዎች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤቶች የተመዘገቡት የነገ ተስፋዎች ማሳያ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የመጋቢታዊያን ፍሬዎች አገርን የሚያሻግሩና ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎች በሁሉም ዘርፎች እየተሠሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በዞኑ “የመጋቢታዊያን ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊ እና በአስተዳደር ዘርፎች እየተካሄዱ ባሉ ሦስቱም መድረኮች ላይ መነሻ የብልጽግና ፓርቲ ዕቅዶች ቀርበው በፐብሊክ ሰርቫንት የፓርቲ አባላት ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በውይይቱ አባላቱ ብልጽግና ፓርቲ የያዛቸው ዕቅዶች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆናቸው ለማሳለጥ በቁርጠኝነት መረባረብ ይገባል ብለዋል።
በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም እና በሌማት ትሩፋቶች እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎችና ሌሎችም ዘርፎች ላይ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን ፐብሊክ ሰርቫንቱ ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ