የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ
በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ 6ኛ የምድብ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት ወደ አሸናፊነት ተመልሷል።
በሞሮኮ አል አብዲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለዋልያዎቹ የማሸነፊያ ግቦችን በረከት ደስታ እና አቡበከር ናስር እያንዳንዳቸው 3 ግቦችን ከመረብ በማሳረፍ ሀትሪክ ሰርተዋል።
በምድብ አንድ የመጀመሪያ ድሉን ያሳካው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ6 ነጥብ ከጊኒ ቢሳው በግብ ክፍያ በልጦ 4ኛ ደረጃን መያዝ ችሏል።
በምድብ ማጣሪያው 5ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው የጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን በበኩሉ በ1 ነጥብ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል