ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ድንቃድን መዝገብ የምስክር ወረቀት ተሰጠው
ፖርቹጋላዊው ኮኮብ ክርስቲያኖ ከሀገሩ ብሔራዊ ቡድን ጋር በርካታ ጨዋታዎችን በማሸነፉ ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ እውቅና ተሰጥቶታል።
የአምስት ጊዜ የባሎንዲኦር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፖርቹጋል ጋር 132 ጨዋታዎችን በማሸነፍ በርካታ ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን ያሸነፈ ቀዳሚው የአለማችን ተጫዋች በመሆኑ ነው እውቅና የተቸረው።
ይህም ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ የተሰጠው አራተኛው እውቅና ሆኗል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከወራት በፊት 901 ጎሎችን በማስቆጠሩ ብዙ የኢንተርናሽናል ጎሎችን ያስቆጠረ ተጫዋች በሚል ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የአንደኛ ደረጃ አትሌትክስ አሰልጣኞች ተመረቁ
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን የክለቡ ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ለማስፈረም ተስማማ
ሶስቱ ብቸኛ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች