ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ድንቃድን መዝገብ የምስክር ወረቀት ተሰጠው
ፖርቹጋላዊው ኮኮብ ክርስቲያኖ ከሀገሩ ብሔራዊ ቡድን ጋር በርካታ ጨዋታዎችን በማሸነፉ ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ እውቅና ተሰጥቶታል።
የአምስት ጊዜ የባሎንዲኦር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፖርቹጋል ጋር 132 ጨዋታዎችን በማሸነፍ በርካታ ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን ያሸነፈ ቀዳሚው የአለማችን ተጫዋች በመሆኑ ነው እውቅና የተቸረው።
ይህም ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ የተሰጠው አራተኛው እውቅና ሆኗል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከወራት በፊት 901 ጎሎችን በማስቆጠሩ ብዙ የኢንተርናሽናል ጎሎችን ያስቆጠረ ተጫዋች በሚል ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ዲሚትሪ ፓዬት ጫማውን ሰቀለ
ቤን ዋይት ከዓመታት በኋላ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ ቀረበለት
ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች የሚካፈሉባቸው ውድድሮች ዛሬይካሄዳሉ