በክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የፀጥታ አካሉ በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ
ቢሮው በክልሉ ለሚገኙ የሰላምና ፀጥታ መምሪያ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በግጭት መከላከል፣ አፈታትና በሰላም ባህል ግንባታ እንዲሁም በግጭት ማስተዳደርና አፈታት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአርባምንጭ እየሰጠ ይገኛል።
”ሠላማችንን በሰላሙ ጊዜ እንስራ” በሚል መሪ ቃል እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ተገኝው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ እና የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ አንቄ እንዳሉት፤ ስልጠናው በክልሉ በሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የግጭት ችግሮችንና አዝማሚያዎችን በመረዳት የሰላም ባህልን ለመገንባት እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
አክለውም ከስልጠናው ጎን ለጎን ሰላምና ፀጥታ፣ ፖሊስና ሚሊሽያ የክልሉ ማህበረሰብ በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት ውይይት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና መልካም አስተዳደርን በክልሉ ለማስፈን በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠው ስልጠና ለቀጣይ ስራ የሚያነሳሳና አሳታፊ እንደሚሆን እምነታቸው መሆኑት አቶ አዲሱ ተናግረዋል።
በስልጠናው በክልሉ የሚገኙ የፖሊስ፣ የሚሊሺያ ዘርፍ ኃላፊዎች፣ የግጭት አፈታት ዘርፍ ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጫ ጣቢያችን
በክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የፀጥታ አካሉ በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል