በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት ንግስት ጌታቸው የብር ሜዳልያ አስገኘች
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የናንጂንግ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ንግስት ጌታቸው ለኢትዮጵያ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
አትሌት ንግስት ጌታቸው ውድድሩን 1 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ ከ63 ማይክሮሴኮንድ በሆነ ሰዓት 2ኛ ደረጃ ይዛ በማጠናቀቅ በሻምፒዮናው ለኢትዮጵያ 3ኛውን የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ አትሌት ፅጌ ድጉማ 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ