በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት ንግስት ጌታቸው የብር ሜዳልያ አስገኘች
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የናንጂንግ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ንግስት ጌታቸው ለኢትዮጵያ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
አትሌት ንግስት ጌታቸው ውድድሩን 1 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ ከ63 ማይክሮሴኮንድ በሆነ ሰዓት 2ኛ ደረጃ ይዛ በማጠናቀቅ በሻምፒዮናው ለኢትዮጵያ 3ኛውን የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ አትሌት ፅጌ ድጉማ 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል