ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በሴቶች 1500 ሜትር ፍፃሜ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እና ደርቢ ወልተጂ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ የሻምፒዮናው ክብረወሰን በሆነ ሰዓት በአንደኝነት አጠናቃ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ድርቤ ወልተጂ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ለሃገሯ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
በዚህም ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ2 የወርቅ እና 2 የብር ሜዳልያዎች ከዓለም 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ