ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በሴቶች 1500 ሜትር ፍፃሜ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እና ደርቢ ወልተጂ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ የሻምፒዮናው ክብረወሰን በሆነ ሰዓት በአንደኝነት አጠናቃ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ድርቤ ወልተጂ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ለሃገሯ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
በዚህም ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ2 የወርቅ እና 2 የብር ሜዳልያዎች ከዓለም 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል