ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በሴቶች 1500 ሜትር ፍፃሜ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እና ደርቢ ወልተጂ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ የሻምፒዮናው ክብረወሰን በሆነ ሰዓት በአንደኝነት አጠናቃ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ድርቤ ወልተጂ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ለሃገሯ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
በዚህም ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ2 የወርቅ እና 2 የብር ሜዳልያዎች ከዓለም 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ