ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
ሀዋሳ: መጋቢት 14/2017 (ደሬቴድ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በሴቶች 1500 ሜትር ፍፃሜ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እና ደርቢ ወልተጂ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ የሻምፒዮናው ክብረወሰን በሆነ ሰዓት በአንደኝነት አጠናቃ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ድርቤ ወልተጂ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ለሃገሯ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።
በዚህም ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ2 የወርቅ እና 2 የብር ሜዳልያዎች ከዓለም 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ