የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የስራ ዘመን 26ኛ መደበኛ ጉባኤ በታርጫ ከተማ እየካሄደ ነው
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዳዊት ሚኖታ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቶች የወከላቸውን ህዝብ ጥቅም ለማስከበር በአስፈፃሚ አካላት የታቀደውን ልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በትክክል ገምግሞ አቅጣጫ ማስቀመጥ ነው።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ አየለ፤ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና የመንግሰት አሰራር ውሰጥ የህዝብ ተሳትፎን በማረጋገጥ በህብረተሰቡ ኑሮ ላይ አዎንታዊ ለውጥና እምርታ እንዲሁም መልካም አሰተዳደር እንዲሰፍን የሚሰሩ ተግባራት የተቋሙ ዓላማ መሆኑን በሪፖርታቸው አንስተዋል።
በቀረበው ሰነድ ላይ በትምህርት ቤቶች አፈፃፀም፣ በማዳበሪያ አቅርቦት እና የእዳ አመላለስ፣ ከኦዲት ግኝት በሚታዩ ችግሮችና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ የምክር ቤት አባላት አስተያየትና ጥያቄ በማንሳት ውይይት እየተደረገ ነው።
ጉባኤው በሚኖረው ቆይታ የምክር ቤትና የዞን አስተዳደር አስፈፃሚ ተቋማት እንዲሁም የፍርድ ቤት የ2017 በጀት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን በመገምገም የተለያዩ ሹመቶችን እንደሚያፀድቅም ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ፡ አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ