የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የስራ ዘመን 26ኛ መደበኛ ጉባኤ በታርጫ ከተማ እየካሄደ ነው
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዳዊት ሚኖታ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቶች የወከላቸውን ህዝብ ጥቅም ለማስከበር በአስፈፃሚ አካላት የታቀደውን ልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በትክክል ገምግሞ አቅጣጫ ማስቀመጥ ነው።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ አየለ፤ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና የመንግሰት አሰራር ውሰጥ የህዝብ ተሳትፎን በማረጋገጥ በህብረተሰቡ ኑሮ ላይ አዎንታዊ ለውጥና እምርታ እንዲሁም መልካም አሰተዳደር እንዲሰፍን የሚሰሩ ተግባራት የተቋሙ ዓላማ መሆኑን በሪፖርታቸው አንስተዋል።
በቀረበው ሰነድ ላይ በትምህርት ቤቶች አፈፃፀም፣ በማዳበሪያ አቅርቦት እና የእዳ አመላለስ፣ ከኦዲት ግኝት በሚታዩ ችግሮችና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ የምክር ቤት አባላት አስተያየትና ጥያቄ በማንሳት ውይይት እየተደረገ ነው።
ጉባኤው በሚኖረው ቆይታ የምክር ቤትና የዞን አስተዳደር አስፈፃሚ ተቋማት እንዲሁም የፍርድ ቤት የ2017 በጀት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን በመገምገም የተለያዩ ሹመቶችን እንደሚያፀድቅም ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ፡ አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል