በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ‘በርግጥም ቲቢን መግታት እንችላለን፤ ቃል በተግባር ሐብት ለውጤት’ በሚል መሪ ቃል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 ዓ.ም የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተጋበዙ እንግዶች እና ተመራማሪዎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዮች በመሣተፍ ላይ ናቸው።
በመድረኩ ቲቢን የተመለከቱ የምርምር ሥራዎች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ