በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ‘በርግጥም ቲቢን መግታት እንችላለን፤ ቃል በተግባር ሐብት ለውጤት’ በሚል መሪ ቃል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 ዓ.ም የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተጋበዙ እንግዶች እና ተመራማሪዎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዮች በመሣተፍ ላይ ናቸው።
በመድረኩ ቲቢን የተመለከቱ የምርምር ሥራዎች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተ
የጋልማ ከተማ አስተዳደር ምስረታ ተካሄደ
በሁሉም ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሴቶች የልማት ህብረትንና የስትሪንግ ኮሚቴ እንቅስቃሴን ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ