በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ‘በርግጥም ቲቢን መግታት እንችላለን፤ ቃል በተግባር ሐብት ለውጤት’ በሚል መሪ ቃል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 ዓ.ም የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተጋበዙ እንግዶች እና ተመራማሪዎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዮች በመሣተፍ ላይ ናቸው።
በመድረኩ ቲቢን የተመለከቱ የምርምር ሥራዎች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅበት ተገለጸ
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ