በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ‘በርግጥም ቲቢን መግታት እንችላለን፤ ቃል በተግባር ሐብት ለውጤት’ በሚል መሪ ቃል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 19ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የ2017 ዓ.ም የዓለም የቲቢ ቀን እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተጋበዙ እንግዶች እና ተመራማሪዎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዮች በመሣተፍ ላይ ናቸው።
በመድረኩ ቲቢን የተመለከቱ የምርምር ሥራዎች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ