ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄን አስመልክቶ ላሳዩት አመራር ‘የአፍሪካ የላቀ አመራር’ ሽልማት የተበረከተላቸው÷ “አፍሪካ የዓለም አቀፍ ንቅናቄ አጣዳፊነት” በሚል መሪ ሐሳብ አሜሪካን አካዳሚ ኦፍ አቺቭመንት እና ግሎባል ሆፕ ኮአሊሽን የተሰኙ ተቋማት በዋሽንግተን ዲሲ በጋራ ባዘጋጁት ልዩ ዝግጅት ላይ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም. የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ስታስጀምር፣ በአራት ዓመታት ውስጥ 20 ቢልየን ችግኞችን ለመትከል ማቀዷ ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያ ከታቀደው ግብ አልፋ በመላ ሀገሪቱ 25 ቢልየን ችግኞች በመትከል የአራት ዓመት ዕቅዷን አሳክታለች።
በዚህም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለደን መልሶ ልማት ላደረገችው አስተዋጽዖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና አግኝታለች።

More Stories
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የቡና ኮንፈረንስ ተጠናቋል
ባህላዊ እሴትና የወንድማማችነት ትስስርን የሚያድስ የ“ኦዴ ኦሶ” ቤተሰብ ምረቃ ስነ-ስርዓት በልዩ ድምቀት ተካሄደ
የጎፋ ዞን ልማት ማህበር ሥራ አመራር ቦርድ የ3ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ