አጀንዳዎችን በማሰባሰብ የህዝቡ ጥያቄ በተገቢው እንዲመለስ የምክክሩ ሂደቱ የላቀ አስተዋፅኦ እንዳለው ተሳታፊዎች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) አጀንዳዎችን በማሰባሰብ የህዝቡ ጥያቄ በተገቢው እንዲመለስ የምክክሩ ሂደቱ የላቀ አስተዋፅኦ እንዳለው ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እየተካሄደ ያለው የአጀንዳ አሰባሰብና ተወካይ መረጣ መቀጠሉን የምክክር ኮሚሽኑ የክልሎች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር እና ዲያስፖራ አስተባባሪ አስታውቀዋል።
የምክክር ሂደቱን አስመልክተው አስተያየት የሰጡን የጌዴኦ ዞን ተሳታፊ መምህር አስራት እሸቱ እና የጎፋ ዞን ተሳታፊ መቶ አለቃ ተፈሪ ጤናው እንደ ሀገር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በሰለጠነ መንገድ መወያየት እና መፍትሄ መፈለግ ይገባል ብለዋል።
መንግስትም የህዝቡን አጀንዳ በመቀበል የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተገቢው በመመለስ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ያሉት ተሳታፊዎቹ የተሻለችውን ኢትዮጵያ ለመገንባት ባህላዊ የግጭት አፈታት ስርአትን ማጎልበት እና ባህላዊ ሸንጎዎችን ማስፋፋት ይገባል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ምክክር ኮሚሽን የ7ቱ ክልሎች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና የዲያስፖራ አስተባባሪ አቶ ረታ ጌራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ2 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች የአጀንዳ አሰባሰብና የተወካይ መረጣ እያካሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ ቀናትም ተፅእኖ ፈጣሪ እና ታዋቂ ሰዎች እንዲሁም የመንግስት አካላት እና የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመክሩበት እና አጀንዳ የሚመርጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
በደቡብ ኢትዮጰያ የምክክር እና የአጀንዳ መረጣ ሂደት ያለምንም ችግር እየተካሄደ መሆኑን የገለፁት አቶ ረታ በክልሉ የሚደረገው ሂደት የተሳካ እንዲሆን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ላበረከው አስተዋፅኦ በኮሚሽኑ ስም አመስግነዋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተደረገ ያለው የምክክ ሂደት በቀጣይ 3 ተከታታይ ቀናት እንደሚቀጥልም ተመላክቷል።
ዘጋቢ ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ