የጂንካ ዩኒቨርስቲ ለኤሶል ልዩ አዳሪ ትምህርት የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ
ዩኒቨርስቲው ከመማር ማስተማር ጎን ለጎ የማህበረሰብ አገልግሎት ተደራሽነት በማስፋት የትምህርት ጥራትንና የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ለውጥ በሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት አድረጎ እየሰራ ነው ።
በርክክብ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባ ጩፋ ዩኒቨርስቲው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የማህበረሰብ አቅፍ አገልግሎት የማጠናከር ሥራ እየሰራ መሆኑን ገለጸው በአሁኑ ድጋፍ ለአዳሪ ትምህርት ቤት በገንዘብ ሲተመን ከ360 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸውን የተለያዩ የጽሕፈት መሣሪያችን ማለትም ኮምፒውተሮችን የማባዣ ማሽኖች እንዲሁም የመኝታ ፍራሾችንና ትራንሶች የውሃ ሮቶዎችን ዩኒቨርስቲው ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል ።
ድጋፉን የተረከቡት የኤሶል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አዝመራ ውድነህ ለድጋፉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ተወካይና የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት አለሙ አይላቴ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ግዴታውን ለመወጣት እየተጋ ነው ብለዋል ፡፡
ምክትል ፕረዚዳንቱ አክለው ለኤሶል ልዩ አዳሪ ት/ቤትከቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ ለትምህርት ቤቱ መምህራን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ እንዲኖራቸው ዩኒቨርስቲው ይደግፋል ሲሉ ተናግረዋል ።
ዘጋቢ ፡ ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መንግሥት ወቅቱን የጠበቀና ጥራት ያለው ውሳኔ እንዲሰጥ የሚያስችል መሆኑን በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
የጎርፍ መውረጃ ቦይ አለመሠራት በቤት ንብረታቸው ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን በከምባታ ዞን የዳምቦያ ከተማ አስተዳደር የ02 ቀበሌ ነዋሪዎች ገለጹ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ከተማ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አደረገ