የጂንካ ዩኒቨርስቲ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ ግምታቸው ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጂንካ ዩኒቨርስቲ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ ለሚዲያ አገልግሎት የሚውሉ ግምታቸው ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ።
የጂንካ ዩኒቨርስቲ የልማትና አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር አለሙ አይለቴ በድጋፉ ወቅት እንደገለፁት፤ የጂንካ ዩኒቨርስቲ ተቋሙን በስልጠና በመደገፍ እየሰራ ካለው ሥራ ባሻገር የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የሚዲያውን ሥራ በውጤታማነት እንዲያከናውን ታስቦ የተደረገ ነው።
ደረጃቸውን የጠበቁ ለሚዲያ ቴክኖሎጂ ሥራ የሚውሉ ዘመናዊ ኮምፒተሮች፣ ዲጅታል የኃይል መቆጣጠሪያ ዩ.ፒ.ኤስ እና ሌሎችም ድጋፍ የተደረጉ ሲሆን አጠቃላይ ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው እንደሆነም ገልፀዋል።
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉዋስ ኢቲሳ በበኩላቸው፤ ዩኒቨርስቲው ላደረገው ድጋፍ አመስግነው ከዚህ ቀደምም ለሚዲያ ባለሙያዎችና በዙሪያው ላሉ የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሙሉ ወጪ ችለው ሰልጠና በማመቻቸት የደገፈ መሆኑን አንስተዋል።
በቀጣይም ከዩኒቨርስቲው ጋር በመቀናጀት ለሚዲያ ባለሙያዎች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ቀደም ብሎ የመግባቢያ ሰምምነት በተፈራረሙት መሠረት እየተሠራ እንዳለ አመላክተዋል።
ዩኒቨርስቲው የሚያደርገውን ሁሉ አቀፍ ድጋፍ በቀጣይም እንዲያጠናክር ሥራ አስኪያጁ ጥሪ አቅርበዋል።
ድጋፉ በተቋሙ ያሉ የግብዓት እጥረቶችን ከመፍታት ባሻገር የሚሰሩ ዜናና ፕሮግራሞች በተሻለ ጥራት እንዲደርስ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የይዘት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ፍቃዱ ግዲ እና የሚዲያ ቴክኖሎጂ የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ በፀጋው ታመነ ናቸው።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት በ2018 በጀት ዓመት በኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ከዞኑ ንግድና ትራንስፖርት መምሪያዎች ጋር የህዝብ አስተያየት ማሰባሰቢያ መድረክ አካሄደ
የወጣቶቻችንን ያልተገደበ ምናብ እና የእጆቻቸውን ጥበብ ወደ ተጨባጭ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መቀየር እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስ፣ የፈጠራ ስራዎች ውድድርና አውደ ርዕይ መካሄድ ጀመረ