የኦሞ ባንክ ኛንጋቶም ቅርንጫፍ በበኩሉ ካለፈው አመት ወዲህ ከ10 ሺህ በላይ የቁጠባ ደንበኞች በማፍራት ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ማስቆጠብ መቻሉን ገልጿል።
ከተቋሙ ደንበኞች መካከል የሊበሬና ሎሬንካቻዎ ቀበሌ ነዋሪ አርብቶ አደር ሶያ ኤጉዋም፣ ኤርምያስ ሎግቸሬ እና ወ/ሮ ናቱኮይ ባይሌ እንደገለጹት በተሰጣቸው ግንዛቤ ተነስተው በግልና በማህበር መቆጠብ ከጀመሩ አስር አመታትን አሳልፈዋል።
በቆይታቸውም ከመቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት ካፒታል ማስመዝገብ፣ ከብቶችና ሞተር ብስክሌት መግዛት፣ ቤት መስራትና ኑሯቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ጠቁመው፤ ተቋሙ ውስጥ ቁጠባቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉና ገንዘብ ለሚያባክኑ አካላትም አርአያነታቸውን እንዲከተሉ መክረዋል።
የኦሞ ባንክ ኛንጋቶም ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳግማዊ መኮንን እንደገለጹት፤ በወረዳው የሚገኘውን አርብቶ አደር ማህበረሰብ የቁጠባ ባህል ለማዳበር ባለፉት አመታት የተሰራው የተቀናጀ ተግባር ውጤት አስገኝቷል ብለዋል።
ከ2016 በጀት አመት ጀምሮም በተቋሙ ከ10 ሺህ 4 መቶ በላይ የቁጠባ ደንበኞችን በማፍራት ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ማስቆጠብ መቻሉን አስረድተዋል።
በ2017 የመጀመሪያው ሩብ አመትም አርባ አምስት አዲስ የቁጠባ ደንበኞች በማፍራት ከ2 መቶ 65 ሺህ ብር በላይ ማስቆጠብ መቻሉንና የሕብረተሰቡ የቁጠባ ባሕል ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ መምጣቱን ስራ ስክያጁ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን ሰይፉ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ