ሀዋሳ፡ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቱ 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2017 ዓ/ም የዞኑ ማስፈፀሚያ በጀት 1 ቢሊዮን 496 ሚሊዮን 511 ሺህ ብር አድርጎ አጽድቋል።
ውስን የሆነውን የመንግስትና የህዝብ ሀብት የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት በሚያስችል መልኩ ተፈፃሚ መሆን እንዳለበት የደቡብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ሎስንዴ ሎኛሱዋ አሳስበዋል።
የህዝቡ አዳጊ ፍላጎቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ እየጨመረ የመጣ በመሆኑ የፀደቀው በጀት ሳይባክን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በልዩ ጥንቃቄ ሊመራ እንደሚገባ የምክር ቤት አባላት በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 ዓ/ም ዕቅድ አፈፃፀምና የ2017 ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ ዝርዝር ውይይት የተካሄደበት ሲሆን፥ በተለይ ፍርድ ቤቶች ገለልተኛ ሆነው ህዝቡን በግልፀኝነት ማገልገል እንዳለባቸው ተጠይቋል።
ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አባላትን የሰየመ ሲሆን፥ ለስድስት የዞን መምሪያ ኃላፊዎች፣ የቱርሚ ከተማ አስተዳደር እና የዳሰነች ወረዳ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳቶች ሹመትም በምክር ቤቱ አባላት ቀርቦ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ