
በአዲስ አበባ ስቴዴየም እስልምና እምነት ተከታዮች የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን በድምቀት እያከበሩ የሚገኙ ሲሆን፥ በበዓሉ ሃይማኖት አባቶች እና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር ኢድሪስ ንግግር አድርገዋል፡፡ በንግግራቸውም የዛሬ ስራችን ቤታችን ያፈራውን እርድን ጨምሮ ሌሎችን በማካፈል የምናስታውሰው ነው ብለዋል፡፡ በስነ ስርዓቱ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነም ለህዝበ ሙስሊሙ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር