
በአዲስ አበባ ስቴዴየም እስልምና እምነት ተከታዮች የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን በድምቀት እያከበሩ የሚገኙ ሲሆን፥ በበዓሉ ሃይማኖት አባቶች እና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር ኢድሪስ ንግግር አድርገዋል፡፡ በንግግራቸውም የዛሬ ስራችን ቤታችን ያፈራውን እርድን ጨምሮ ሌሎችን በማካፈል የምናስታውሰው ነው ብለዋል፡፡ በስነ ስርዓቱ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነም ለህዝበ ሙስሊሙ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ አፀደቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበለትን የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አፀደቀ
የእናቶችና ህፃናት ሞት ለመቀነስ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ውጤት እየተገኘባቸው እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ