
በአዲስ አበባ ስቴዴየም እስልምና እምነት ተከታዮች የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን በድምቀት እያከበሩ የሚገኙ ሲሆን፥ በበዓሉ ሃይማኖት አባቶች እና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር ኢድሪስ ንግግር አድርገዋል፡፡ በንግግራቸውም የዛሬ ስራችን ቤታችን ያፈራውን እርድን ጨምሮ ሌሎችን በማካፈል የምናስታውሰው ነው ብለዋል፡፡ በስነ ስርዓቱ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነም ለህዝበ ሙስሊሙ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

More Stories
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ አገልግሎት ያስገነባቸውን ዘመናዊ ኮምፕሌክሶችን አስመረቀ
በጎፋ ዞን ወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጋ ማጠቃለያና የክረምት በጎ ስራ ማስጀመሪያ መረሃ-ግብር ተካሄደ
በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ሀብት መሰብሰብ መቻሉ ተገለጸ