የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጂ ያሲን ከድርን ጨምር የአሪ ዞን አስተዳደር ተወካይን፣ የዞንና የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
የአሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ማታዶ በርቢ የሚመሰረተው ምክር ቤት ለሠላምና አንድነት ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልፀዋል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳደር ተወካይ አቶ ተመስገን ተረፈ የህዝቡ ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥም የድርሻውን የሚያበረክት ይሆናል ብለዋል፡፡
የህዝቦችን አንድነት እንዲጠናከር ያግዛል ያግዛል ያሉት ደግሞ የአሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ምክትል አፈጉ ባኤ አቶ ሲሳይ ጋልሺ ናቸው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ-ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
የምሁራን አንድነትን ማጠናከርና የእርስ በእርስ መከባበር ባህልን ማጎልበት ለአካባቢው ዘላቂ ሠላም መስፈን ወሳኝነት እንዳለው ተመላከተ
በብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስተባባሪዎችና ዕጩ ወኪሎች ኃላፊነትና ግዴታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
የመምህራንን ኑሮ ለማሻሻል እና ሙያዊ ክብራቸውን ለመመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ለዊ ተናገሩ