የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጂ ያሲን ከድርን ጨምር የአሪ ዞን አስተዳደር ተወካይን፣ የዞንና የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
የአሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ማታዶ በርቢ የሚመሰረተው ምክር ቤት ለሠላምና አንድነት ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልፀዋል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳደር ተወካይ አቶ ተመስገን ተረፈ የህዝቡ ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥም የድርሻውን የሚያበረክት ይሆናል ብለዋል፡፡
የህዝቦችን አንድነት እንዲጠናከር ያግዛል ያግዛል ያሉት ደግሞ የአሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ምክትል አፈጉ ባኤ አቶ ሲሳይ ጋልሺ ናቸው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ-ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ