የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጂ ያሲን ከድርን ጨምር የአሪ ዞን አስተዳደር ተወካይን፣ የዞንና የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
የአሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ማታዶ በርቢ የሚመሰረተው ምክር ቤት ለሠላምና አንድነት ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልፀዋል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳደር ተወካይ አቶ ተመስገን ተረፈ የህዝቡ ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥም የድርሻውን የሚያበረክት ይሆናል ብለዋል፡፡
የህዝቦችን አንድነት እንዲጠናከር ያግዛል ያግዛል ያሉት ደግሞ የአሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ምክትል አፈጉ ባኤ አቶ ሲሳይ ጋልሺ ናቸው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ-ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ