ሀዋሳ፡ ጥር 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የፍትህ ሚኒስቴር በአዲሱ የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባምንጭ እያካሔደ ነው።
የፍትህ ማሻሻያው፥ የፍትህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲሠሩ ያግዛልም ተብሏል።
ፍኖተ ካርታውን ቀድመው ተግባራዊ ባደረጉ አካባቢዎች የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ አቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቃባ ተናግረዋል።
የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ቀደም ሲል በስራ ላይ የነበረው የፍትህ ስርዓት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ፣ ግልጽነት እና ተጠያቅነትን ይበልጥ በማስፈን የተገልጋይን እርካታ ለመጨመር ያግዛል ያሉት በፍትህ ሚኒስቴር የሪፎርም ዘርፍ ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ኤርሚያስ የማነ ብርሐን ናቸው።
በመድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳን ጨምሮ የፍትህ ተቋማት ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ