ሀዋሳ፡ ጥር 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የፍትህ ሚኒስቴር በአዲሱ የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባምንጭ እያካሔደ ነው።
የፍትህ ማሻሻያው፥ የፍትህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲሠሩ ያግዛልም ተብሏል።
ፍኖተ ካርታውን ቀድመው ተግባራዊ ባደረጉ አካባቢዎች የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ አቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቃባ ተናግረዋል።
የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ቀደም ሲል በስራ ላይ የነበረው የፍትህ ስርዓት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ፣ ግልጽነት እና ተጠያቅነትን ይበልጥ በማስፈን የተገልጋይን እርካታ ለመጨመር ያግዛል ያሉት በፍትህ ሚኒስቴር የሪፎርም ዘርፍ ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ኤርሚያስ የማነ ብርሐን ናቸው።
በመድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳን ጨምሮ የፍትህ ተቋማት ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ባህል በማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ