ሀዋሳ፡ ጥር 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የፍትህ ሚኒስቴር በአዲሱ የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባምንጭ እያካሔደ ነው።
የፍትህ ማሻሻያው፥ የፍትህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲሠሩ ያግዛልም ተብሏል።
ፍኖተ ካርታውን ቀድመው ተግባራዊ ባደረጉ አካባቢዎች የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ አቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቃባ ተናግረዋል።
የፍትህ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ቀደም ሲል በስራ ላይ የነበረው የፍትህ ስርዓት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ፣ ግልጽነት እና ተጠያቅነትን ይበልጥ በማስፈን የተገልጋይን እርካታ ለመጨመር ያግዛል ያሉት በፍትህ ሚኒስቴር የሪፎርም ዘርፍ ሚኒስቴር ደኤታ ዶ/ር ኤርሚያስ የማነ ብርሐን ናቸው።
በመድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳን ጨምሮ የፍትህ ተቋማት ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ