የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ለስራ ጉዳይ ወደ ውብቷ ወላይታ ሶዶ ገብተዋል።
ሚኒስትሯ ወደ ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ሲገቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሳምነው አይዛን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በወላይታ ሶዶ የሚካሄደው 9ኛው ኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን እየጎበኙ ናቸው ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዘግቧል፡፡

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ