የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ለስራ ጉዳይ ወደ ውብቷ ወላይታ ሶዶ ገብተዋል።
ሚኒስትሯ ወደ ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ሲገቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሳምነው አይዛን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በወላይታ ሶዶ የሚካሄደው 9ኛው ኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን እየጎበኙ ናቸው ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዘግቧል፡፡

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ