ጠንካራ ባህላዊ መዋቅር በመኖሩና ህዝቡም ተግባራዊ በማድረጉ ሥርዓቱ እንደ ችግር መፍቻነት እያገለገለ እንደሚገኝ የጌዴኦ የባህል አባት አባገዳ ቢፎሚ ዋቆ ገለጹ
የአካባቢው ማህበረሰብም ከአባገዳው የሚተላለፉ ባህላዊ መመሪያዎችን ተቀብለን በመተግበራችን ተጠቃሚ ሆነናል ሲሉም ተናግረዋል።
ብሔሩ በሚተዳደርበት ባህላዊ በ”ባሌ” ስርዓት መሠረት ከየአካባቢው የተውጣጡ የህዝብ እንደራሴዎች ስለ ህዝቡ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊውም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች በመመካከር በአባገዳው አማካይነት አዋጅ እንዲተላለፍ የሚደረግ ጠንካራ ባህላዊ መዋቅር ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ አባገዳው ገልጸዋል።
የሚተላለፉ አዋጆች ወይም መመሪያዎች የህዝብን የዕለት ተዕለት እንቅሰቃሴን መሠረት ያደረጉ በመሆናቸው ለተግባሮቻቸው አጋዥ እንደሚሆኑም አስረድተዋል።
ከጥንት ጀምሮ እሰከዛሬ ጠብቀው በመምጣታቸው በአካባቢው ሠላምን፣ ልምላሜን፣ አንድነትንና ሌሎች ትሩፋቶችን ለመጎናጸፍ መቻላቸውን የተናገሩት አባገዳው ስርዓቱ ዛሬም እነዚህን ፋይዳዎች ለማስቀጠል የጎላ ሚና አንዳለውም አስገንዝበዋል።
የዞኑ ነዋሪዎችም ከአባገዳው የሚተላለፉ መመሪያዎችን ተቀብለን በመተግበራችን ተጠቃሚ ሆነናል ሲሉም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ