ጠንካራ ባህላዊ መዋቅር በመኖሩና ህዝቡም ተግባራዊ በማድረጉ ሥርዓቱ እንደ ችግር መፍቻነት እያገለገለ እንደሚገኝ የጌዴኦ የባህል አባት አባገዳ ቢፎሚ ዋቆ ገለጹ
የአካባቢው ማህበረሰብም ከአባገዳው የሚተላለፉ ባህላዊ መመሪያዎችን ተቀብለን በመተግበራችን ተጠቃሚ ሆነናል ሲሉም ተናግረዋል።
ብሔሩ በሚተዳደርበት ባህላዊ በ”ባሌ” ስርዓት መሠረት ከየአካባቢው የተውጣጡ የህዝብ እንደራሴዎች ስለ ህዝቡ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊውም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች በመመካከር በአባገዳው አማካይነት አዋጅ እንዲተላለፍ የሚደረግ ጠንካራ ባህላዊ መዋቅር ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ አባገዳው ገልጸዋል።
የሚተላለፉ አዋጆች ወይም መመሪያዎች የህዝብን የዕለት ተዕለት እንቅሰቃሴን መሠረት ያደረጉ በመሆናቸው ለተግባሮቻቸው አጋዥ እንደሚሆኑም አስረድተዋል።
ከጥንት ጀምሮ እሰከዛሬ ጠብቀው በመምጣታቸው በአካባቢው ሠላምን፣ ልምላሜን፣ አንድነትንና ሌሎች ትሩፋቶችን ለመጎናጸፍ መቻላቸውን የተናገሩት አባገዳው ስርዓቱ ዛሬም እነዚህን ፋይዳዎች ለማስቀጠል የጎላ ሚና አንዳለውም አስገንዝበዋል።
የዞኑ ነዋሪዎችም ከአባገዳው የሚተላለፉ መመሪያዎችን ተቀብለን በመተግበራችን ተጠቃሚ ሆነናል ሲሉም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው