በ2016 በተደረገዉ ንቅናቄ በክልል ደረጃ 75 በመቶ የጤና መድን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መቻሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የክልሉ ጤና ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት 6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የጤና መድህን ያለበትን ደረጃ የገመገመ ሲሆን እስከአሁን በአባልነት የተመዘገቡት ቁጥራቸዉ ወደ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን በመሆኑን በክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህክምና አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምትኩ ታመነ ገልጸዋል።
በዚህም መክፈል የሚችሉ ራሳቸዉ እንደሚከፍሉና መክፈል የማይችሉት ተለይተዉ በወረዳ፣ በዞንና በክልሉ መንግስት የሚሽፈን መሆኑንም ተናግረዋል።
ከነባር አባላት እድሳት አኳያ እስከአሁን ባለው ሂደት በዞኖች ደረጃ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡት ኮንታ፣ ሸካ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ መሆናቸው ተመላክቷል።
በተካሄደዉ ግምገማ መሻሻሎች መታየታቸዉን የገለፁት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በአንድ ሳምንት ውስጥ በተካሄደዉ ንቅናቄ የጤና መድህን አባልነት ቁጥር መጨመሩን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አባይነሽ ወራቦ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ