ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጥራት ያለው የጤና አገለግሎት ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል የሁሉም የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የግማሽ አመት የጤና ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ጉባኤ በታርጫ ከተማ በመከናወን ላይ ይገኛል።
በጉባኤ የተገኙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም ጥራት ያለው የጤና አገለግሎት ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል የሁሉም የባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።
የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበዬሁ በበኩላቸው የመድኃኒትና የጤና ግብአት አቅርቦት ተደራሽነት ለማሻሻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ጉባኤው በባለፉት ስድስት ወራት በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠልና በጉድለት የተገመገሙ ጉዳዮችን ማሻሻልን አላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በጉባኤው የክልል፣ የዞኖች፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አባይነሽ ወራቦ- ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ