ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጥራት ያለው የጤና አገለግሎት ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል የሁሉም የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የግማሽ አመት የጤና ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ጉባኤ በታርጫ ከተማ በመከናወን ላይ ይገኛል።
በጉባኤ የተገኙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም ጥራት ያለው የጤና አገለግሎት ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል የሁሉም የባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።
የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበዬሁ በበኩላቸው የመድኃኒትና የጤና ግብአት አቅርቦት ተደራሽነት ለማሻሻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ጉባኤው በባለፉት ስድስት ወራት በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠልና በጉድለት የተገመገሙ ጉዳዮችን ማሻሻልን አላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በጉባኤው የክልል፣ የዞኖች፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አባይነሽ ወራቦ- ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ