ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሃገር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ትላልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናገሩ።
የግብርና ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በአርባ ምንጭ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ባለፉት ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል።
በተለይ በበልግ እርሻ ወቅት ጥሩ የሚባል ጊዜን ማሳለፍ እንደተቻለና በአነስተኛ ማሳ ጭምር 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መልማቱን ጠቅሰዋል።
በመስኖ ልማት ሥራም ባለፉት ሁለት እና ሶስት ወራት ወደ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን አብራርተዋል።
በሌማት ትሩፋት ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ እንዲሁም ከማዳበሪያ ግዢና ስርጭት ጋር ያሉ አፈጻጸሞች መልካም ስለመሆናቸው አንስተዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አፈጻጸምን ጨምሮ የሌሎች ብሄራዊ ክልሎች የዘርፉ አፈጻጸም እየቀረበ ነው።
ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመልስ
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው