ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሃገር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ትላልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናገሩ።
የግብርና ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በአርባ ምንጭ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ባለፉት ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል።
በተለይ በበልግ እርሻ ወቅት ጥሩ የሚባል ጊዜን ማሳለፍ እንደተቻለና በአነስተኛ ማሳ ጭምር 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መልማቱን ጠቅሰዋል።
በመስኖ ልማት ሥራም ባለፉት ሁለት እና ሶስት ወራት ወደ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን አብራርተዋል።
በሌማት ትሩፋት ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ እንዲሁም ከማዳበሪያ ግዢና ስርጭት ጋር ያሉ አፈጻጸሞች መልካም ስለመሆናቸው አንስተዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አፈጻጸምን ጨምሮ የሌሎች ብሄራዊ ክልሎች የዘርፉ አፈጻጸም እየቀረበ ነው።
ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመልስ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ