ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሃገር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ትላልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናገሩ።
የግብርና ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በአርባ ምንጭ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በሁሉም የግብርና ዘርፎች ባለፉት ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል።
በተለይ በበልግ እርሻ ወቅት ጥሩ የሚባል ጊዜን ማሳለፍ እንደተቻለና በአነስተኛ ማሳ ጭምር 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መልማቱን ጠቅሰዋል።
በመስኖ ልማት ሥራም ባለፉት ሁለት እና ሶስት ወራት ወደ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን አብራርተዋል።
በሌማት ትሩፋት ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ እንዲሁም ከማዳበሪያ ግዢና ስርጭት ጋር ያሉ አፈጻጸሞች መልካም ስለመሆናቸው አንስተዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አፈጻጸምን ጨምሮ የሌሎች ብሄራዊ ክልሎች የዘርፉ አፈጻጸም እየቀረበ ነው።
ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመልስ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ