ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወልቂጤ ዩኒቨርስቲና በሠላም ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀ የውይይት መድረክ “አድዋን ለዘላቂ ልማትና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል::
በመድረኩ ላይ የተገኙት በሠላም ሚኒስቴር የመንግስታት ግንኙነት ዴስክ ሀላፊ አቶ ግርማ ቸሩ እንደተናገሩት የአድዋ ድልን መዘከር በየትኛውም መስክ ለተሰማራው ዜጋ፣ ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት፣ ሠላምና ዘላቂ እድገት በአድዋዊ የአንድነትና የድል አድራጊነት መንፈስ እንዲተጋ የማነሳሳት ፋይዳ አለው::
ኃላፊው አክለውም የአድዋ ድል ለመላው አፍሪካዊያንና ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት መሆኑን ገልፀዋል::
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፉሪስ ደሊል በበኩላቸው በቀደምት ጀግኖች አባቶች ከተገኘው ድል አዲሱ ትውልድ የአንድነት መንፈስን በመማር ውስጣዊ ችግሮችን በምክክር መድረክ በመፍታት በኢትዮዽያ ዘላቂ ሠላም፣ ልማትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል::
በውይይት መድረኩ የአድዋ ታሪካዊ ገጽታ፣ የሀገርና ሀገረ መንግስት ግንባታና እሴቶች ላይ ያተኮሩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠኑ ጥናታዊ ጽሁፎች በምሁራን ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል::
ከጥናታዊ ጽሁፍ አቅራቢዎች መካከል በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ በቃሉ ዋቺሶ እንደገለፁት በጀግና አባቶች ደም የተገኘውን የድል ፍሬ ይህ ትውልድም ድሉን በተግባር ማስቀጠል ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡
በምክክር መድረኩ በቀረቡ ጥናታዊ ጽሁፎች ላይ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ በቀረቡ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው የውይይት መድረኩ ተጠናቋል::
ዘጋቢ፡ መሀመድ ጀማል

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ