ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የግብርና ሚኒስቴር፣ የተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የግማሽ አመት አፈጻጸሙን የሚገመግም መድረክ በአርባ ምንጭ ያካሂዳል።
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) አርባምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በጋሞ አባቶች ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃይለማርያም ተስፋዬና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ለቀጣይ ቀናት በሚደረገው በዚሁ የግምገማ መድረክ የሁሉም ክልሎች የግማሽ አመት አፈፃፀምን ጨምሮ ቀጣይ የዘርፉ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ወንድወሰን ሽመልስ
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/