ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የግብርና ሚኒስቴር፣ የተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የግማሽ አመት አፈጻጸሙን የሚገመግም መድረክ በአርባ ምንጭ ያካሂዳል።
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) አርባምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በጋሞ አባቶች ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃይለማርያም ተስፋዬና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ለቀጣይ ቀናት በሚደረገው በዚሁ የግምገማ መድረክ የሁሉም ክልሎች የግማሽ አመት አፈፃፀምን ጨምሮ ቀጣይ የዘርፉ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ወንድወሰን ሽመልስ
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው