ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የግብርና ሚኒስቴር፣ የተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የግማሽ አመት አፈጻጸሙን የሚገመግም መድረክ በአርባ ምንጭ ያካሂዳል።
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) አርባምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በጋሞ አባቶች ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃይለማርያም ተስፋዬና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ለቀጣይ ቀናት በሚደረገው በዚሁ የግምገማ መድረክ የሁሉም ክልሎች የግማሽ አመት አፈፃፀምን ጨምሮ ቀጣይ የዘርፉ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ወንድወሰን ሽመልስ

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ