ሀዋሳ፡ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የግብርና ሚኒስቴር፣ የተጠሪ ተቋማትና የክልሎች የ2016 በጀት የግማሽ አመት አፈጻጸሙን የሚገመግም መድረክ በአርባ ምንጭ ያካሂዳል።
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) አርባምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በጋሞ አባቶች ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃይለማርያም ተስፋዬና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ለቀጣይ ቀናት በሚደረገው በዚሁ የግምገማ መድረክ የሁሉም ክልሎች የግማሽ አመት አፈፃፀምን ጨምሮ ቀጣይ የዘርፉ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ወንድወሰን ሽመልስ

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ