አስተዳዳሪው ይህን የተናገሩት የጎፋ ዞን የስፖርት ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ነው።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት ፋንታዬ ስፖርት በዓለም ላይ ራሱን የቻለ ትልቅ ኢንዱስትሪ መሆኑን ገልጸዋል።
ዘርፉን ኢኮኖሚ የሚመነጭበት፣ ሠላምና አንድነት የሚሰበክበት እንዲሆን በማድረግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጠቀሜታ ለማስፋት ሁለም የድርሻውን ሊያበረክት ይገባል ብለዋል።
ለስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎችን በማዘጋጀትና በማስፋፋት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
የጎፋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊና የምክር ቤቱ ፀሐፊ አቶ አወቀ ዓለሙ በበኩላቸው በዞኑ ከ 75 በላይ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖራቸው የተደረገ ቢሆንም ሌሎች ጉድለቶችን ለቅሞ ማረም እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል።
የስፖርቱን የውድድር መድረኮችን መነሻ በማድረግ በዞኑ በቋሚና በጊዜያዊ ለ74 ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።
በጉባኤው የጎፋ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሥራ ኃላፊዎች፣ የወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እና የስፖርት ፌዴሬሽን አመራሮች ተገኝተዋል።
በጉባኤው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች እንዲሁም የወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤቶች የዋንጫ እና መዳሊያ ሽልማት ተበርክቷል
ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ቅርጫፍ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ