አስተዳዳሪው ይህን የተናገሩት የጎፋ ዞን የስፖርት ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ነው።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት ፋንታዬ ስፖርት በዓለም ላይ ራሱን የቻለ ትልቅ ኢንዱስትሪ መሆኑን ገልጸዋል።
ዘርፉን ኢኮኖሚ የሚመነጭበት፣ ሠላምና አንድነት የሚሰበክበት እንዲሆን በማድረግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጠቀሜታ ለማስፋት ሁለም የድርሻውን ሊያበረክት ይገባል ብለዋል።
ለስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎችን በማዘጋጀትና በማስፋፋት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
የጎፋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊና የምክር ቤቱ ፀሐፊ አቶ አወቀ ዓለሙ በበኩላቸው በዞኑ ከ 75 በላይ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖራቸው የተደረገ ቢሆንም ሌሎች ጉድለቶችን ለቅሞ ማረም እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል።
የስፖርቱን የውድድር መድረኮችን መነሻ በማድረግ በዞኑ በቋሚና በጊዜያዊ ለ74 ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።
በጉባኤው የጎፋ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሥራ ኃላፊዎች፣ የወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እና የስፖርት ፌዴሬሽን አመራሮች ተገኝተዋል።
በጉባኤው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች እንዲሁም የወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤቶች የዋንጫ እና መዳሊያ ሽልማት ተበርክቷል
ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ቅርጫፍ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ