ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመለከቱ
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የተመራ ልዑክ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በከተማው የተሰራውን የመሰረተ ልማት ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት እንደገለፁት የህዝባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የብልፅግና ጉዞን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራችንን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
በጉብኝቱ መርሃ ግብር የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎን፣ የክልልና የዞን የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምንጭ ፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው