ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመለከቱ
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የተመራ ልዑክ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በከተማው የተሰራውን የመሰረተ ልማት ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት እንደገለፁት የህዝባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የብልፅግና ጉዞን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራችንን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
በጉብኝቱ መርሃ ግብር የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎን፣ የክልልና የዞን የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምንጭ ፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ