ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመለከቱ
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የተመራ ልዑክ በወንዶ ገነት ከተማ እየተሰሩ የሚገኙትን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በከተማው የተሰራውን የመሰረተ ልማት ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት እንደገለፁት የህዝባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የብልፅግና ጉዞን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራችንን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
በጉብኝቱ መርሃ ግብር የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎን፣ የክልልና የዞን የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምንጭ ፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ