የሴቶች የንቅናቄ መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የኢትዮጵያን ሰላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አስረክባለሁ” በሚል መሪ ቃል የሴቶች የንቅናቄ መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ ላይ የክልሉና የዞን አመራር አካላት እንዲሁም በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ሴቶችና በዞኑ የሚገኙ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የሴቶች ሊግ አካላት ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ቆይታ የሀገርን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ ረገድ ሴቶች መወጣት በሚገባቸው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ይደረጋል ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሳሙኤል መንታሞ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ