የሴቶች የንቅናቄ መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የኢትዮጵያን ሰላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አስረክባለሁ” በሚል መሪ ቃል የሴቶች የንቅናቄ መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ ላይ የክልሉና የዞን አመራር አካላት እንዲሁም በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ሴቶችና በዞኑ የሚገኙ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የሴቶች ሊግ አካላት ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ቆይታ የሀገርን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ ረገድ ሴቶች መወጣት በሚገባቸው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ይደረጋል ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሳሙኤል መንታሞ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ