አካዳሚው ብቃት ያላቸው መሪዎችን ለማፍራት ዓልሞ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ አስታወቀ
አካዳሚው ለክልሉ ወጣቶችና ለሴቶች አደረጃጀት አመራሮች በየም ዞን ሳጃ ከተማ እየሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንደቀጠለ ነው።
የአካዳሚው ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የስልጠና ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብድልበር ዑስማን ወጣቶቹ ሀገራዊ ተልዕኮን የሚፈጽሙና የሚያስፈጽሙ ትልቅ አደራን ተሸክመው የሚንቀሳቀሱ ናቸው ብለዋል።
አካዳሚው እየሰጠ ያለው ስልጠና በአመራሩ ላይ የሚታዩ የአመለካከት ውስንነትን የሚቀርፍበት፣ ከራስ አልፎ ለሌሎች መኖርን የሚለማመዱበት፣ በአርበኝነት ተልዕኮአቸውን የሚፈጽሙበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጸናበት ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብላቱ ያለ ብቁ መሪ እድገትም፣ ብልጽግናም፣ ልማትም ሊታሰብ እንደማይችል ነው የጠቆሙት።
ለሁሉም ለውጦች መሠረቱ መሪዎች መሆናቸውን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ ብቃት ያላቸው መሪዎችን ለማፍራት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና ነው እየሰጠን የምንገኘው ብለዋል።
የመደመር ትውልድ ብዙ የተመሠቃቀሉ ጉዳዮችን የሚያስተካክል የነገ ራዕይ፣ ትልሞች እና እቅዶችን የሚያቃና መሆኑም አቶ ተስፋዬ ብላቱ ገልጸዋል።
በአካዳሚው ያገኙት ስልጠና ስለ አንድ ጠንካራ አመራር ሊያሟላቸው የሚገቡ እውቀትና ሊያዳብራቸው የሚገቡ ክህሎትን የተገነዘቡበት መሆኑን ሰልጣኞች ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ