የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የበጋ መስኖ ልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።
በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ፣ በብልፅግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው በሸበዲኖ ወረዳ በአርሶ አደሮች እና በማህበር በተደራጁ ወጣቶች በበጋ መስኖ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል።
የሸበዲኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኤልያስ አየለ በወረዳው በዘንድሮ የበጋ መስኖ ሥራ 2ሺህ 885 ሄክታር መሬት በቲማቲም፣ በጥቅል ጎመን፣ በሽንኩርትና በተለያዩ ሰብሎች እየለማ መሆኑን ተናግረዋል።
ወጣቶችን በግብርና ልማት ሥራ ላይ በስፋት ለማሰማራት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በመስኖ ሥራ ብቻ 135 ወጣቶችን በማሳተፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የክልሉ አመራሮች ከሸበዲኖ ወረዳ በተጨማሪ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ እና ሌሎች አካባቢዎች ያሉ የመስኖ ልማት ሥራዎችንም ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።(ኢዜአ)

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ