የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የበጋ መስኖ ልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።
በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ፣ በብልፅግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው በሸበዲኖ ወረዳ በአርሶ አደሮች እና በማህበር በተደራጁ ወጣቶች በበጋ መስኖ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል።
የሸበዲኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኤልያስ አየለ በወረዳው በዘንድሮ የበጋ መስኖ ሥራ 2ሺህ 885 ሄክታር መሬት በቲማቲም፣ በጥቅል ጎመን፣ በሽንኩርትና በተለያዩ ሰብሎች እየለማ መሆኑን ተናግረዋል።
ወጣቶችን በግብርና ልማት ሥራ ላይ በስፋት ለማሰማራት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በመስኖ ሥራ ብቻ 135 ወጣቶችን በማሳተፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የክልሉ አመራሮች ከሸበዲኖ ወረዳ በተጨማሪ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ እና ሌሎች አካባቢዎች ያሉ የመስኖ ልማት ሥራዎችንም ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።(ኢዜአ)

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ