ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ፋቱ ሀይድራናን የዩኒዶ ኢትዮጵያ(UNIDO,Ethiopia) የስራ ኃላፊዎችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ስለ ድርጅቱ ድጋፍ ስኬቶችና በስራ ሂደት ስላጋጠሙ ችግሮች ኢንዲሁም ቀጣይ ስለሚደረጉ የትብብር ማዕቀፎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡
ሚኒስትሩ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የአምራች ኢንዱስትሪውን ለመደገፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው ዘርፉ በተሻለ ሁኔታ የሚጠበቅበትን ሀገራዊና አለማቀፋዊ እድገት ያሳካ ዘንድ ድጋፉ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
በውይይቱ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የኢትዮጵያ የስራ ሪፖርት በኢትዮጵያ የድርጅቱ ተወካይ እና ቀጠናዊ ዳይሬክተር ኦሬሊያ ፓትሪዢያ ካላብሮ ቀርቦ ውይይት መደረጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ