ሚኒስትሩ ዩኒዶ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠየቁ

ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ፋቱ ሀይድራናን የዩኒዶ ኢትዮጵያ(UNIDO,Ethiopia) የስራ ኃላፊዎችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ስለ ድርጅቱ ድጋፍ ስኬቶችና በስራ ሂደት ስላጋጠሙ ችግሮች ኢንዲሁም ቀጣይ ስለሚደረጉ የትብብር ማዕቀፎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡

ሚኒስትሩ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የአምራች ኢንዱስትሪውን ለመደገፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው ዘርፉ በተሻለ ሁኔታ የሚጠበቅበትን ሀገራዊና አለማቀፋዊ እድገት ያሳካ ዘንድ ድጋፉ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡

በውይይቱ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የኢትዮጵያ የስራ ሪፖርት በኢትዮጵያ የድርጅቱ ተወካይ እና ቀጠናዊ ዳይሬክተር ኦሬሊያ ፓትሪዢያ ካላብሮ ቀርቦ ውይይት መደረጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡