ከ800 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የቡና ኮንፍረንስና ኤግዚቪሽን እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ከ800 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የመጀመሪያው “የአፍሪካ የቡና ሳምንት በኢትዮጵያ” እና 20ኛው የአፍሪካ ኮፊ አሶሴሽን ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን ከጥር 28 እስከ የካቲት 2/2016 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
ለአንድ ሳምንት በሚቆየው ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን የ25 ቡና ላኪ አፍሪካ ሀገራትና የቡና ገዢ ሀገራት የግብርና ሚኒስትሮች ተጋብዘዋል።
በኮንፍረንስና ኤግዚብሽኑ ድርጅቶች ምርታቸውን እንደሚያስተዋውቁ፤ ዝርዝር ጥናቶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው እና በጅማና ሃዋሳ የጉብኝት መርሃግብር እንደሚኖር ተገልጿል።(ኢፕድ)

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ
ከ2 ሺህ በላይ አዲስ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን መታቀዱን የሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቃ