መምሪያው በ2ዐ16 በጀት ዓመት 6 ወራት አፈፃፀም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
በመክፈቻ መድረኩ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ዋና እንስፔክተር ደበበ ኦንቶ፤ ፖሊስ የዞኑን ሠላም ለማስጠበቅ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት እያደረገ ያለውን አኩሪ አድንቀዋል።
በቀጣይም ህብረተሰቡን ከጎኑ በማሰለፍ ለዘላቂ ሠላም እና የህግ የበላይነት ማስከበር በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ያስፈልጋል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ወንጀል እንዲከላከል ስለ ወንጀል አስከፊነት ትምህርቶችን ከመስጠት ባሻገር በህገወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን በመከታተል ለህግ የማቅረቡ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል የፖሊስ አዛዡ።
በስድስት ወራት ውስጥ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 18 ሽጉጥ፣ 54 የሽጉጥ ጥይት፣ 6 ክላሽ ጠመንጃ፣ 325 ኋላቀር የጦር መሳሪያ፣ 8 ጥይት፣ 60 ኤፍ ዋን ቦምብ ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ተናግረዋል።
በመድረኩ ከሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የፖሊስ አዛዦች እና የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል አስተባባሪዎች የተሳተፉ ሲሆን የ2016 በጀት ዓመት 6 ወራት አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡ ንጋቷ ይስሀቅ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክረምቱ ወቅት የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም ከማስቻሉም በላይ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጅት ከፍተኛ እገዛ እያደረገላቸው መሆኑን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ገለፁ
ብሔራዊ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የተሻለ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚጠቅም ተገለጸ
በክልሉ በ2018 በጀት አመት ከ336 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ከምዝበራና ከብክነት ማዳን መቻሉ ተገለጸ