ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ለወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ500 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የመድሃኒትና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉ የማይክሮስኮፕ እና 25 አይነት መድሃኒቶችና የህክምና ቁሳቁስ ያካተተ ነው።
የተደረገው ድጋፍ በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የሴቶችና ህጻናት የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ግልጋሎት ለማጠናከር የሚውልነው ተብሏል፡፡
የፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኃላፊና የፍትሐ ብሄርና ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገብሬ አስፋው የአንድ ማዕከል አገልግሎት (One Stop Center) አላማ ወሲባዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በአንድ ጣሪያ ስር የተቀናጀ የጤና፣ የፍትህ፣ የሰነልቦናና ማህበራዊ አገልግሎት መስጠት እና በቀጣይ የሚያሰፈልጋቸውን አገልግሎቶች በቅብብሎሽ ስርዓት እንዲያገኙ ማድረግ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢክማ ሁሴን ከቢሮው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ