ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ለወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ500 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የመድሃኒትና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉ የማይክሮስኮፕ እና 25 አይነት መድሃኒቶችና የህክምና ቁሳቁስ ያካተተ ነው።
የተደረገው ድጋፍ በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የሴቶችና ህጻናት የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ግልጋሎት ለማጠናከር የሚውልነው ተብሏል፡፡
የፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኃላፊና የፍትሐ ብሄርና ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገብሬ አስፋው የአንድ ማዕከል አገልግሎት (One Stop Center) አላማ ወሲባዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በአንድ ጣሪያ ስር የተቀናጀ የጤና፣ የፍትህ፣ የሰነልቦናና ማህበራዊ አገልግሎት መስጠት እና በቀጣይ የሚያሰፈልጋቸውን አገልግሎቶች በቅብብሎሽ ስርዓት እንዲያገኙ ማድረግ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢክማ ሁሴን ከቢሮው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/