ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ለወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ500 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የመድሃኒትና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉ የማይክሮስኮፕ እና 25 አይነት መድሃኒቶችና የህክምና ቁሳቁስ ያካተተ ነው።
የተደረገው ድጋፍ በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የሴቶችና ህጻናት የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ግልጋሎት ለማጠናከር የሚውልነው ተብሏል፡፡
የፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኃላፊና የፍትሐ ብሄርና ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገብሬ አስፋው የአንድ ማዕከል አገልግሎት (One Stop Center) አላማ ወሲባዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በአንድ ጣሪያ ስር የተቀናጀ የጤና፣ የፍትህ፣ የሰነልቦናና ማህበራዊ አገልግሎት መስጠት እና በቀጣይ የሚያሰፈልጋቸውን አገልግሎቶች በቅብብሎሽ ስርዓት እንዲያገኙ ማድረግ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢክማ ሁሴን ከቢሮው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ