ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) አራት ፌስታል አደንዛዥ እፅ በተሽከርካሪ ጭነው ሲያዘዋውሩ የተገኙ አምስት ግለሰቦች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ለቡ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ግለሰቦቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-26732 አ.አ በሆነ ተሽከርካሪ በአራት ትልልቅ ፌስታል ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ እፅ ጭነው ሲያዘዋውሩ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎችን ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ለወንጀል መንስኤ በሆኑና አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ጫት መቃሚያ ቤቶች እንዲሁም ቁማር ቤቶች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተከታታይነት ያለው እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
በተለይም ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን የመከላከሉ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማስገኘት እንዲችል የህብረተሰቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ