ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) አራት ፌስታል አደንዛዥ እፅ በተሽከርካሪ ጭነው ሲያዘዋውሩ የተገኙ አምስት ግለሰቦች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ለቡ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ግለሰቦቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-26732 አ.አ በሆነ ተሽከርካሪ በአራት ትልልቅ ፌስታል ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ እፅ ጭነው ሲያዘዋውሩ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎችን ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ለወንጀል መንስኤ በሆኑና አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ጫት መቃሚያ ቤቶች እንዲሁም ቁማር ቤቶች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተከታታይነት ያለው እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
በተለይም ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን የመከላከሉ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማስገኘት እንዲችል የህብረተሰቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ