ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) አራት ፌስታል አደንዛዥ እፅ በተሽከርካሪ ጭነው ሲያዘዋውሩ የተገኙ አምስት ግለሰቦች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ለቡ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ግለሰቦቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-26732 አ.አ በሆነ ተሽከርካሪ በአራት ትልልቅ ፌስታል ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ እፅ ጭነው ሲያዘዋውሩ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪውን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎችን ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ለወንጀል መንስኤ በሆኑና አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ጫት መቃሚያ ቤቶች እንዲሁም ቁማር ቤቶች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተከታታይነት ያለው እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
በተለይም ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን የመከላከሉ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማስገኘት እንዲችል የህብረተሰቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ